top of page

መጋቢት 25፣2016 - ከ2 ወር በላይ ያህል ታግዶ የቆየው የመሬት አገልግሎት እግድ ተነሳ

  • sheger1021fm
  • Apr 3, 2024
  • 1 min read

በመሬት ልማትና አስተዳደር በተጠናው የመዋቅር ጥናት የሰራተኞች ድልድል ተካሂዶ ምደባ እስከሚካሄድ ድረስ ከጥር 21/2016 ዓ.ም ጀምሮ የመሬት አገልግሎት ታግዶ መቆየቱ ይታወሳል።


አጠቃላይ የሰራተኛ ድልድሉ በመጠናቀቁ ከመጋቢት 23፣2016 ዓ/ም ጀምሮ የመሬት አገልግሎት መጀመሩን የከተማዋ መሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ተናግሯል።


የመሬት እግድ አልግሎቱ መነሳቱን በተመለከተም የቢሮው ሃላፊ አቶ ሲሳይ ጌታቸው ለሁሉም ከፍለ ከተሞች በላኩት ደብዳቤ አስረድተዋል።


ቢሮው ከዚህ በፊት የነበረውን ብልሹ አሰራር ለማስቀረት ሲባል አዲስ ሥርዓት ዘርግቶ፤ የመሬት ይዞታ አገልግሎት መዝገቦች ሁሉ ዲጂታል አድርጌአለሁ ማለቱ አይዘነጋም፡፡



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





ShegerFM: @ShegerFMRadio102_1

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page