top of page

መጋቢት 21፣2016 - የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ከሰነደ ሙዓለ ነዋይ ገበያ የ60 ሚሊዮን ብር አክሲዮን መግዛቱን ተናገረ

  • Mar 30, 2024
  • 1 min read

የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ከኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ነዋይ ገበያ የ60 ሚሊዮን ብር አክሲዮን መግዛቱን ተናገረ።


ባንኩ ከገበያው የ60 ሚሊየን ብር ድርሻ የገዛው በትናንትናው ዕለት መሆኑን ለሸገር በላከው መግለጫ ተናግሯል

በዚህም የኦሮሚያ ኅብረት ስራ ባንክ የገበያው መስራች አባል መሆን ችሏል።


ባንኩ የ60 ሚሊዮን ብር ድርሻ ከኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ነዋይ ገበያ የገዛው ገበያው በሀገሪቱ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋትና ተጨማሪ የፋይናንስ እድሎችን ለመፍጠር የተቋቋመ መሆኑን በመገንዘብ ነው ብሏል።


ባንኩ የገዛው አክሲዮን ለህብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊ ልማት የሚያከናውናቸውን ተግባራት በመደገፍ በኩል ትልቅ ሚና ይኖረዋል ሲልም በመግለጫው አስረድቷል።

የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ነዋይ ገበያ ከእቅዱ ቀድሞ ለማሰባሰብ ካቀደው የመመስረቻ ካፒታል 1 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን መናገሩ ይታወሳል፡፡


መስራች የሚያደርገው የአክሲዮን ሽያጭ ቀነ ገደብ በትላንትናው እለት አብቅቷል፡፡


ገበያው በቅርቡ ስራ ይጀምራ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ለተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች፣ የኢንቨስትመንት ፈንድ ለማሰባሰብና ሌሎች ዘመናዊ የግብይቶችን ለማካሄድ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል ተብሎ ታምኖበታል፡፡


ንጋቱ ሙሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
በኢትዮጵያ በቆዳና ሌጦ ዘርፍ ሲሰሩ ከነበሩ 31 ፋብሪካዎች ውስጥ አሁን በስራ ላይ ያሉት ሰባት ብቻ ናቸው ተባለ።

ሐምሌ 16 2018 በኢትዮጵያ በቆዳና ሌጦ ዘርፍ ሲሰሩ ከነበሩ 31 ፋብሪካዎች ውስጥ አሁን በስራ ላይ ያሉት ሰባት ብቻ ናቸው ተባለ። ይህን ያለው የኢትዮጵያ ጥሬ ቆዳ እና ሌጦ አቅራቢዎች ማህበር ነው ። እነዚህ ፋብሪካዎች የወጡት በግብር እና በቫት መጨመር እንደሆነም ማህበሩ ነግሮናል። ፋብሪካዎቹ ላይ ቫት እንዲጨመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page