top of page

መጋቢት 17 2017 - ብሔራዊ ባንክ በኢኮኖሚ ውስጥ የተጠናከረው ለውጥ አለ ቢልም እኛ የጠየቅናቸው ባለሞያ በዚህ አይስማሙም

  • sheger1021fm
  • Mar 26
  • 1 min read

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ በዳግም ስብሰባው የገንዘብ አቅርቦት፣ የፋይናንስ ዘርፍ እንቅስቃሴዎችን፣ የገንዘብ ዝውውር፣ የፊስካል፣ የዋጋ ግሽበት እና አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታውን ገምግሟል።


አሁን ያለውን 15 በመቶ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በመጪዎቹ ወራቶች ቅናሽ እንዲያሳይ ጥንቃቄ የተሞላበት አካሄድን መከተል አስፈላጊ መሆኑንን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ተናግሯል፡፡


ለዚህም ሲባል #የብሔራዊ_ባንክ የፖሊሲ ተመን አሁን ባለበት እንዲቀጥል ተወስኗል፡፡


ማዕከላዊ ባንኩ የዋጋ ግሽበት እየቀነሰ መምጣቱን ተናግሮ በየካቲት ወር መጨረሻም 15 በመቶ ደርሷል ብሏል።


ባንኩ የገንዘብ ሁኔታን ገምግሜያለሁ ካለ በኋላ የገንዘብ ዝውውሩ በኢኮኖሚ ውስጥ የተጠናከረ እድገት አሳይቷል ይላል።

ree

በዚህ መግለጫ ማዕከላዊ ባንኩ ስለ ውጭ ምንዛሪ አስተዳደር በተለይ በመደበኛው እና በትይይዩ ገበያ ያለውን ልዩነት በዝርዝር አላስረዳም።


ብሔራዊ ባንክ በኢኮኖሚ ውስጥ የተጠናከረው ለውጥ አለ ቢልም እኛ የጠየቅናቸው ባለሞያ በዚህ አይስማሙም።


አብዱልመናን መሀመድ(ዶ/ር) በኢትዮጵያ ኢኮኖሚና ፋይናንስ የ ፒኤችዲ ወረቀት ፅፈዋል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… https://0fj.cc/gcZ9SquRbdr


ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r


Recent Posts

See All
በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡

ታህሳስ 6 2018 በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ የአካባቢው ቡሣ ጎኖፋ ወይም የእርዳታ ማስተባበሪያ በበኩሉ ድጋፍ እንዲቀጥል ለሚመለከተው የበላይ አካል ባሳውቅም ድጋፍ ግን ሊቀጥል አልቻለም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page