top of page

መጋቢት 12 2017 - ደንቡ ሙሉ ለሙሉ ተፈፃሚ የሚሆነው ዝርዝር የአፈፃፀም መመሪያ ሲወጣለት መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ተናገረ

  • Mar 21, 2025
  • 1 min read

አገልግሎት ሰጪዎች እስከ ምሽት 4:00 እንዲሰሩ ለማድረግ የወጣው ደንብ ሙሉ ለሙሉ ተፈፃሚ የሚሆነው ዝርዝር የአፈፃፀም መመሪያ ሲወጣለት መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ተናገረ፡፡


በከተማዋ የኮሪደር ልማት በተሰራባቸው አካባቢዎች ሱቆች እና ሌላም የንግድ አገልግሎት ሰጭዎች እስከ ምሽት በራቸውን እንዳይዘጉ ወይም በራቸው ዝግ ከሆነ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት በራቸው ላይ እንዲያኖሩ የሚያስገድደው ደንብ ከመጋቢት 10 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ስራ ገብቷል ተብሎ ነበር፡፡


የከተማ አስተዳደሩ የደንቡን አተገባበር አስመልክቶ ከነጋዴው ማህበረሰብ ጋር በዛሬው ዕለት ባደረገው ውይይት ከነጋዴው ወገን በርካታ ቅሬታዎች ተነስተዋል።


አምሽተን ስንወጣ የስራና የመኖሪያ ቦታችን የተራራቀ በመሆኑ የደህንነት ስጋቶች አሉብን፤ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ሱቃችንን ብንዘጋ፤ በድንገት መብራት ቢጠፋ በደምቡ ላይ በር እንዳይዘጋ ማብራት እንዳይጠፋ የሚል ስለተቀመጠ ብቻ መቀጣት የለብንም የሚሉና መሰል ጥያቄዎች ተጠይቀዋል።


ውይይቱን የመሩት የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ዣንጥራር አባይ በሰጡት ምላሽ ስጋታችሁን እንረዳለን የወጣው ደንብ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ የሚሆነው ዝርዝር የአፈፃፀም መመሪያ ሲወጣለት ነው ብለዋል።


ምንታምር ፀጋው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Recent Posts

See All
አስተማማኝ የጤና ሥርዓት ለመገንባት በሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርትን ማጠናከርና የፀረ-ተሕዋስያን መድኃኒቶችን አጠቃቀም ቁጥጥር ማጠናከር እንዲሁም የፋርማሲ ዘርፍ ጥናትና ምርምር ማሳደግ ያስፈልጋል ተባለ።

ሐምሌ 22 2018 አስተማማኝ የጤና ሥርዓት ለመገንባት በሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርትን ማጠናከርና የፀረ-ተሕዋስያን መድኃኒቶችን አጠቃቀም ቁጥጥር ማጠናከር እንዲሁም የፋርማሲ ዘርፍ ጥናትና ምርምር ማሳደግ ያስፈልጋል ተባለ። አስተማማኝ የጤና ሥርዓት ለመገንባት ኢትዮጵያ በመድኃኒት ምርት ራሷን መቻል እንዳለባት፣ በተ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page