top of page

መስከረም 9 2018 - አስረኛው የኢትዮጵያ የከተሞች ፎረም ህዳር ወር ላይ በሠመራ ሎጊያ ከተማ እንደሚካሄድ ተነገረ።

  • sheger1021fm
  • Sep 19
  • 1 min read

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሣኒ ፎረሙን አስመልክተው ዛሬ በመስሪያ ቤታቸው ጋዜጣዊ መግለጫ ስጥተዋል።


በመግለጫቸውም አስረኛው የኢትዮጵያ የከተሞች ፎረም ከህዳር 6 እስከ 10 ቀን 2018 ዓም በአፋር ክልል ይካሄዳል ብለዋል።


በፎረሙ ላይ ከ150 እስከ 200 የሚደርሱ ከተሞች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።


የልምድ ልውውጥ በከተሞች መካከል ይኖራል የተባለ ሲሆን ጥናቶችና ምርምሮች ቀርበው ውይይት እንደሚካሄድባቸውም ተጠቅሷል።


እያንዳንዱ ከተማ የሠራውን ስራና ያገኘውን ውጤት የሚያሳይበት ኤግዚቢሽንም እንደሚኖር ሚኒስትሯ በመግለጫው ላይ ተናግረዋል።


የዘንድሮው የከተሞች ፎረም በአፋር ክልል የሚካሄደው "የከተሞች ዕድገት ፣ ለኢትዮጵያ ልህቀት"በሚል ሀሳብ እንደሆነም ተነግሯል።


ፎረሙን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ከአፋር ክልል መንግስት ጋር በመተባበር ያዘጋጁታል ተብሏል ።


ዘጠነኛው የኢትዮጵያ የከተሞች ፎረም አምና በሶዶ ከተማ ነበር የተዘጋጀው።


ንጋቱ ረጋሳ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page