top of page

መስከረም 7፣2017 - በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በከፍተኛ ኤሌክትሪክ ሀይል ተጠቃሚዎች ላይ ቀድሞ ይከፍሉት ከነበረው በኪሎ ዋት የ95 ብር ከ87 ሳንቲም ጭማሪ መደረጉ ተረጋገጠ

  • sheger1021fm
  • Sep 17, 2024
  • 1 min read

በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በከፍተኛ ኤሌክትሪክ ሀይል ተጠቃሚዎች ላይ ቀድሞ ይከፍሉት ከነበረው በኪሎ ዋት የ95 ብር ከ87 ሳንቲም ጭማሪ መደረጉ ተረጋገጠ፡፡


የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ላይ ደግሞ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የተደረገው ጭማሪ 26 ብር ከ34 ሳንቲም መሆኑን ሰምተናል፡፡


ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ሀይል ያገኘነው መረጃ እንደሚያሳየው በስራ ላይ በቆየው ታሪፍ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚዎች በኪሎ ዋት 157 ብር ከ16 ሳንቲም ይከፍሉ ነበር፡፡


በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በተደረገው ጭማሪ መሰረት ደግሞ በኪሎ ዋት 183 ብር ከ51 ሳንቲም እንዲከፍሉ ተደርጓል፡፡


ይህም በኪሎ ዋት ከ26 ብር በላይ ጭማሪ እንዲከፍሉ ያደረገ መሆኑን ያሳያል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል የተሳሳተ ዘገባ በመሆኑ ይታረምልኝ ባለው ትናንት በሰራነው ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዘገባ በኪሎ ዋት ከ95 ብር በላይ ጭማሪ መደረጉን አምኖ ይህ ጭማሪ ግን ከፍተኛ የሀይል ተጠቃሚ ለሆኑ ፋብሪካዎች ነው ብሏል፡፡


በየሩብ ዓመቱ የታሪፍ ጭማሪ ይደረጋል የተባለ ሲሆን በ4 ዓመት ውስጥ 40 በመቶ ጭማሪ ይደረጋል ተብሏል፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page