top of page

መስከረም 6 2018 - በኢትዮጵያ በአዲሱ ዓመት ስለ ሠላም ከመመኘት ያለፈ ቁርጠኛ ስራ ይጠይቃል ተባለ።

  • sheger1021fm
  • Sep 16
  • 1 min read

ኢትዮጵያ የጠንካራ ሀገረ መንግስት ታሪክ ያላት ሀገር እንደ መሆኗ ሁሉ ጠንካራ የተቃዋሚ ኃይሎች ታሪክ ያላት ሀገር በመሆኗ ሠላምና መረጋጋትን ለማምጣት በአዲሱ ዓመት ስለ ሠላም ከመመኘት ያለፈ ቁርጠኛ ስራ ይጠይቃል ተባለ።


የሀገርን ሠላምና መረጋጋት በማምጣት ሂደት ውስጥ ሰፊ ድርሻ ያላቸው የሲቪክ ማህበራት፤ ሠላምን በማስፈን በኩል የሚሰሩት ስራ በተበታተነ አደረጃጀትና በተናጠል ነው የተባለ ሲሆን ከዚህ በኋላ በተጠናከረ ህብረት ለሰላም መቆም አለባቸው ሲባልም ሰምተናል።

ree

ይህ የተባለው የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ባዘጋጀው ሃገር አቀፍ የሰላም ኮንፈረንስ ላይ ነው።


ኮንፈረሱ "በአዲሱ ዓመት ሰላም የሰፈነባት ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ሲሆን የሃገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣የሲቪክ ማህበራት፣የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮችና ሌሎች ተሳትፈውበታል።


መድረኩ ሁሉንም የሚመለከታቸውን በማሰባሰብ ለሰላም መደፍረስ ዋና ዋና ምክንያቶች ላይ ለመወያየት፣ በሰላም ግንባታ ጥረቶች የተገኙ ውጤቶችን ለመዳሰስ፣ እንዲሁም ዘላቂ ሰላም እና የተረጋጋ የወደፊት ጉዞን በትብብር ለማቀድ የተዘጋጀ መድረክ ነው ተብሏል።


ንጋት መኮንን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page