top of page

መስከረም 5 2018 - የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት ተፈታኞች የሚያገኙባቸውን አድራሻዎች የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጓል።

  • sheger1021fm
  • Sep 15
  • 1 min read

የ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት ተፈታኞች የሚያገኙባቸውን አድራሻዎች የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጓል።


ተፈታኞች ውጤታቸውን በዌብ ሳይት፤ በቴሌግራም ወይም በአጭር የፅሁፍ መልዕክት አድራሻዎች ዛሬ ከሰዓት ጀምሮ ማየት ይችላሉ ብሏል አገልግሎቱ፡፡


አድራሻዎቹም ለዌብ ሳይት፡ result.eaes.et


ለቴሌግራም፡ t.me/EAESbot እና


አጭር የጽሑፍ መልዕክት 6284 መሆናቸውን አመልክቷል።


ዌብ ሳይትና ቴሌግራም አድራዎችን የሚጠቀሙ ተፈታኞች ጊዜያዊ ሰርቲፊኬታቸውን ወዲያውኑ መውሰድ(download በማድረግ) እና መጠቀም ይችላሉ ብሏል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page