መስከረም 30 2018 - ''የትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎች ምደባ ቀስ በቀስ ይቆማል ያሉት'' ብርሃኑ ነጋ ፕ/ር
- sheger1021fm
- Oct 10
- 1 min read
ዩኒቨርሲቲዎች ስለተማሪዎቻቸው ትክክለኛ መረጃ ካላቀረቡ ፕሬዝዳንቱን ጨምሮ ሀላፊዎቻቸው ከስራ ይባረራሉ ተባለ።
ይህንን ያሉት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ናቸው።
በቀጣይ 6 ወራት ዩኒቨርሲቲዎች ስለተማሪዎቻቸውና ሌሎችም ጉዳዮች መረጃ በትክክል ለትምህርት ሚኒስቴር ማቅረብ አለባቸው ተብሏል።
ይህንን ያላደረገ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት በስራው አይቀጥልም ብለዋል።
ይህንን ስራ እኔ በቀጥታ እከታተለዋለሁ ሲሉም የትምህርት ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት የትምህርት ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር የዩኒቨርስቲ ውጤት በተመለከተ የስምምነት ውል በተፈራረመበት ወቅት ነው።
የትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎች ምደባ ቀስ በቀስ ይቆማል ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፣ ዩኒቨርስቲዎች በራሳቸው ጥረት ተማሪዎችን መቀበል ይጀምራሉ ብለዋል።
በቅርብ ጊዜ ውስጥ እኛ የተማሪ ምደባ ስራን እየቀነስን እንመጣለን፣ ያ ሲሆን ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲ መርጠውና በተቋሙ ብቃት ለይተው መግባት ይጀምራሉ ብለዋል።
በረከት አካሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s
👔LinkedIn ፡ https://tinyurl.com/tyfaekvx












Comments