መስከረም 28 2018 - የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት የመጀመሪያ የሆነው ቅርንጫፍ ዛሬ አገልግሎት ጀምሯል ተባለ፡፡
- sheger1021fm
- Oct 8
- 1 min read
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት የመጀመሪያ የሆነውን ቦሌ ቅርንጫፍ በዛሬው ዕለት አገልግሎት አስጀምረዋል::
የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት በ12 የከተማው ተቋማት ስር ያሉ 96 አገልግሎቶች በጋራ አገልግሎት የሚሰጡበት መሆኑንና ሁለት ባንኮች እና 4 የፌደራል ተቋማትም መካተታቸውን አስረድተዋል::

በቅርቡ ሶስት የፌደራል ተቋማትን ወደ ማዕከሉ እንደሚያካትት እና በቀጣይ 9 ተጨማሪ ቅርንጫፎችን ለመክፈት እንዳቀደም ሰምተናል::
የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ቅልጥፍና፣ የደንበኞችን እርካታ ይጨምራል ተብሎ ታምኖበታል፡፡
አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት የተለያዩ ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎቶች በዲጂታል እና በቴክኖሎጂ በመታገዝ በአንድ ማዕከል ውስጥ እየሰጡ እንደሆነም ሰምተናል፡፡
ማርታ በቀለ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s
👔LinkedIn ፡ https://tinyurl.com/tyfaekvx












Comments