top of page

መስከረም 28 2018 11ኛው የአፍሪካ አሰላሳዮች (ቲንክ - ታንክ) ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ፡፡

  • sheger1021fm
  • Oct 8
  • 1 min read

ጉባኤው"ከግብር ወደ ተግባር" በሚል መሪ ሀሳብ መካሄድ የጀመረ ሲሆን እስከ ከነገ ወዲያ ድረስ ይቆያል፡፡


በሶስት ቀናቱ ውሎ በአፍሪካ በህዝብ ሀብት አስተዳደር ላይ ያሉ የፖሊሲ አፈጻጸም ችግሮች ላይ ይመክራል፣ ሀሳብ ይዋጣል ተብሏል፡፡


300 አሰላሳዮች ( #Think_Tank ) ፖሊሲ አውጪዎች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች፣ የግሉ ዘርፍ መሪዎች፣ የልማት አጋሮች ከ50 ሀገራት ተወክለው እየተሳተፉ እንደሆነ ሰምተናል፡፡

ree

አፍሪካ እንዴት አድርጋ ያለ ውጭ ጣልቃ ገብነት ሀብቷን ታስተዳድር፣ እንደ ታክስ ያሉ ህጎችን ታውጣ፣ እንዴትስ አድርጋ ወጪዎችን ትቻል አንዲሁም እዳዋልን ትከፍላለች በሚሉት ነጥቦች፣ በፖሊሲ ቁረጠኝነትና አፈጻጸም መካከል ያለውን ክፍተት መድፈን ይቻላል የሚሉት የጉባኤው መወያያ ጉዳዮች መሆናቸውን ተነግሯል፡፡


የህዝብ ሀብት ለማስተዳደር ፈተና ሆነው የቀጠሉ የፖሊሲ ማነቆዎች እንዴት መፈተታት አለባቸው፣ የውጭ እርዳታ ጥገኝነትን መቀነስ እንዲሁም አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት የሚያስፈልጉትን ሀብቶች ለማሰባሰብ ምን ማድረግ ይገባል የሚሉትም የጉባኤው የትኩርት ጉዳዮች ናቸው፡፡


ጉባኤውን የአፍሪካ አቅም ግንባታ ፋውንዴሽን(ACBF) ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን (AUC) እና የአፍሪካ አመራር የልህቀት አካዳሚ ጋር በመተባበር አንዳዘጋጁት ሰምተናል፡፡


ንጋቱ ሙሉ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page