top of page

መስከረም 24፣2016 - ለኢሬቻ በዓል አስፈላጊ ዝግጅቶች ተደርገዋል ተባለ

  • sheger1021fm
  • Oct 5, 2023
  • 1 min read

የፊታችን ቅዳሜ በአዲስ አበባ፣ በማግስቱ እሁድ ደግሞ በቢሾፍቱ ለሚከበረው የኢሬቻ በዓል አስፈላጊ ዝግጅቶች ተደርገዋል ተባለ።


የኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ሃይሉ አዱኛ የተደረጉ ዝግጅቶችን አስመልክተው ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።


በመግለጫቸው እንዳሉት በዓሉ እሴቱን ጠብቆ በሠላም እንዲከበር በየደረጃው ያሉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ውይይት አካሂደዋል።

ree

የክልሉ፣ የአዲስ አበባ እና የፌዴራል የፀጥታ አካላትም በዓሉ በሠላም እንዲከበር ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን ተናግረዋል።


የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የሚሰጡ ወጣቶች እንዲሁ ህዝቡን ለማስተባበር እና ለመርዳት ተዘጋጅተዋል ብለዋል።


የአዲስ አበባ፣ የሸገር ከተማ እና የቢሾፍቱ ከተማ ነዋሪዎችም እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት እንደጨረሱ አቶ ሃይሉ ተናግረዋል።


በዓሉ ወደ ሚከበርባቸው ቦታዎች የየትኛውንም ፖለቲካ ፓርቲ አርማ ይዞ መሄድ በጥብቅ የተከለከለ መሆኑ በመግለጫው ወቅት ተነግሯል።


ከፀጥታ አካላት እና የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ከሚሰጡ ወጣቶች ጋር መተባበር እንደሚያስፈልግም በኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ቢሮ ግቢ ውስጥ በተሰጠው በዚሁ መግለጫ ላይ ተነስቷል።


በዚህ መልኩም በዓሉ በሠላም ተጀምሮ በሠላም እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን ሃላፊነት እንዲወጣ የቢሮ ሃላፊው ጥሪ አቅርበዋል።



ንጋቱ ረጋሣ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page