top of page

መስከረም 22 2018 - እንደ መሬት ፅ/ቤት ያሉ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ተገልጋዩን በማንገላታት ብዙውን ጊዜ ይወቀሳሉ፡፡

  • sheger1021fm
  • Oct 2
  • 1 min read

እንደ መሬት ፅ/ቤት ያሉ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ተገልጋዩን በማንገላታት ብዙውን ጊዜ ይወቀሳሉ፡፡


የሚሰጡ አገልግሎቶችን ቅልጥፍና ይጨምራል፣ የደንበኞችን እርካታ ይጨምራል በሚል የአንድ መሶብ አገልግሎት ተጀምሯል፡፡


አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት የተለያዩ ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎቶች በዲጂታል እና በቴክኖሎጂ በመታገዝ በአንድ ማዕከል ውስጥ እየሰጡ እንደሆነም ሰምተናል፡፡


13 ተቋማትን ይዞ የጀመረው ማዕከሉ 107 አገልግሎቶች እንዳሉትም ሰምተናል፡፡


13ቱ ተቋማት በሶስት ዘርፍ የተከፈሉ እንደሆኑና በዚህም የኢኮኖሚ ዘርፍ፣ የቤቶችና ትራንስፖርት ዘርፍ፣ እንዲሁም የመሬት እና ግንባታ ዘርፍ እንደሆኑ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ ተናግረዋል፡፡


የመሶብ ሲስተም እዚሁ ሃገር ውስጥ በኢትዮጵያ አርተፊሻል ኢንተለጀስ ኢንስቲትዩት የለማ ነው ተብሏል፡፡

አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት የሚገኘው በአዲስ አበባ ከተማ የቀደሞ አራዳ ክ/ከተማ የነበረበት ህንጻ ላይ ነው፡፡


ወደፊት ዘጠኝ ቅርንጫፎችን እንደሚከፍት ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ዮናስ አለማየሁ ተናግረዋል፡፡


ማርታ በቀለ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page