top of page

መስከረም 20 2018 - አቢሲኒያ ባንክ በተጠናቀቀው በጀት አመት 10.1 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ አገኘሁ አለ

  • sheger1021fm
  • Sep 30
  • 1 min read
ree
ree

ይህም ካለፈው የሒሳብ ዓመት የ91.4 በመቶ ጭማሬ ማሳየቱን ተናግሯል።

አቢሲኒያ ባንክ ይህንን የተናገረው 29ኛ የባለአክስዮኖች መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ነው።


በተጠናቀቀው የሒሳብ አመት ባንኩ ያገኘው የውጭ ምንዛሬ መጠን 663 ሚሊየን ዶላር መሆኑን የተናገረ ሲሆን ይህም ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ56.4 ጭማሬ አሳይቷል ብሏል።


አጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑም ከ192.5 ቢሊዮን ብር ወደ 243.2 ቢሊዮን ብር ማድረስ ተችሏል የተባለ ሲሆን ከተሰበሰበው ተቀማጭ ገንዘብ ውስጥ የቁጠባ ሒሳብ ድርሻ 65.2 በመቶ መያዙ ተነግሯል።


ከወለድ ነፃን ሳይጨምር ለደንበኞች የሰጠሁት ብድር 193.4 ቢሊየን ብር ደርሷል ማለቱን በሪፖርቱ የሰማን ሲሆን ካለፈው ሒሳብ ዓመት የብድርና ቅድመ ክፍያዎች ጋር ሲመሳከር የ30.5 ቢሊዮን ብር ጭማሬ እንዳለው ተነግሯል።

ባንኩ ካለው የብድር ክምችት ውስጥ የወጭ ንግድ፣ ኢንዱስትሪ እና የሀገር ውስጥ ንግድ የሥራ ዘርፎች 64.2 በመቶውን ይሸፍናል መባሉ ሲነገር ሰምተናል።


በ2017 የሒሳብ አመት የአቢሲኒያ ባንክ ጠቅላላ ወጭ 29 ቢሊዮን ብር ሆኖ መመዝገቡ በሪፖርቱ የተነገረ ሲሆን  ጠቅላላ ሀብቱም 286.2 ቢሊዮን ደርሷል ተብሏል።


በተጠናቀቀው በጀት አመት የባንኩ አጠቃላይ ካፒታል ወደ 28.8 ቢሊዮን ብር ከፍ ማለቱን የሰማን ሲሆን ይህም ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረው ጋር ሲነፃፀር የ5.7 ቢሊዮን ብር ወይም የ24.4 በመቶ እድገት አለው ተብሏል።


እንዲሁም የባንኩ የተከፈለ ካፒታል መጠን ባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ከተመዘገበው 14.2 ቢሊዮን ብር ወደ 15 ቢሊዮን ብር በማደግ 794 ሚሊዮን ወይም የ5.6 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱ ተነግሯል።


ፋሲካ ሙሉወርቅ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page