መስከረም 19 2018 - የ2018 የኢሬቻ በዓል የፊታችን ቅዳሜ በአዲስ አበባ ፣ በቀጣዩ ቀን እሁድ ደግሞ በቢሾፍቱ እንደሚከበር ተነገረ
- sheger1021fm
- Sep 29
- 1 min read

በዓሉ ኢሬቻ ለሀገር ማንሰራራት በሚል ሀሳብ ይከበራል ተብሏል።
የኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ በበዓሉ አከባበር ላይ ያተኮረ ስልጠና ስቴዲየም በሚገኘው የኦሮሞ ባህል ማዕከል ለጋዜጠኞች እየሰጠ ነው።
ኢሬቻ የምስጋና እና የዕርቅ በዓል ነው ያሉት የኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ሃይሉ አዱኛ በአከባባሩ ላይ ሰዎች በሃይማኖት ፣ በብሄር ፣ በፆታ ወዘተ ልዩነት እንደማይደረግባቸውም ተናግረዋል ።
የኢሬቻ በዓል ከማህበራዊ ቱሩፋቶቹ ባሻገር ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታም ያለው ነው ብለዋል ።
የኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ጀሚላ ሲምቢሩ በበኩላቸው በዓሉ ዕሴቱን ጠብቆ እንዲከበር የመገናኛ ብዙሃን ባለሞያዎች ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
ንጋቱ ረጋሳ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX








