መስከረም 16 2018 - ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የኒውክሌር ልማት ፕሮጀክት ስምምነት መፈራረማቸው ተሰማ
- sheger1021fm
- Sep 26
- 1 min read

ሩሲያ እና ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ልማት ዙሪያ በሮሳቶም እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መካከል የድርጊት መርሃ ግብር ተፈራረመዋል ሲል ስፑትኒክ ዘግቧል።
የሮሳቶም ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሌክሲ ሊካቼቭ እና የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ የተፈረመውን ሰነድ ተለዋውጠዋል።
በዝግጅቱ ላይም ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ተገኝተዋል ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወደ ሩሲያ የሄዱት በዓለም የአቶሚክ ሣምንት ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ መሆኑ ተነግሯል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ የኒውክለር ኃይልን በጥንቃቄ በማቀድና ጥቅም ላይ በማዋል ጠንካራ የሀገር ውስጥ አቅምን በመፍጠር ለሰላማዊ ዓላማ ለመጠቀም ማቀዷን አስረድተዋል ።
የሩሲያን የኒውክለር ጠበበቶች ከኢትዮጵያ የተማረ ሰው ሃይል ጋር በማጣመር ለሕዝብ የሚጠቅምና ለአፍሪካ ተምሳሌት የሆነ የኒውክለር ቴክኖሎጂ ለመገንባት መታቀዱን ጠቅሰዋል ፡፡
ከዚሁ ወሬ ጋር በተያያዘ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተወያይተዋል።
መሪዎቹ የኃይል ማመንጫ፣ ግብርና፣ የጤና ጥበቃ ልማት እና የመከላከያ ትብብርን ጨምሮ ሰፊ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስረድቷል።
ውይይቱ ለማኅበረሰብ አገልግሎት ንፁህ ኃይል ምንጭ የሚውል የጋራ የኒውክሊየር ኃይል ማመንጫ የማልማት ስምምነቶችን ጨምሮ የጋራ ፍላጎት በሆኑ ጉዳዮች ላይ መካሄዱም ተነግሯል።
ኢትዮጵያ ለሰላማዊ አለማ የሚሆን የኒውክለር ፕላት እንደምታቋቁም በአደስ አመት ዋዜማ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ መናገራቸው ይታወሳል።
ይህንን የኢትዮጵያ ፍላጎትም የዓለም አቀፉ የአቶሚክ ሀይል ተቆጣጣሪ ኤጀንስ ይደግፈዋል መባሉ ይታወሳል።
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX











It was immediately evident that she wasn’t Escort in Indore only stunning but also thoughtful, graceful, and considerate, making sure every detail of our time was tailored perfectly to my enjoyment.