top of page

መስከረም 14 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች

  • sheger1021fm
  • Sep 24
  • 1 min read
ree

ጀርመን የወታደሮቿን ብዛት እና የመከላከያ ወጪዋን በእጅጉ ልትጨምር ነው ተባለ፡፡


አገሪቱ በብዙ ሺህዎች የሚቆጠሩ ወታደሮችን ለመመልመል መሰናዳቷን አሶሼትድ ፕሬስ ፅፏል፡፡


ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የጀርመን የጦር አቅም ማደርጃ ውጥን ደጋግሞ እየተሰማ ነው፡፡

የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት /ኔቶ/ አባል አገሮቹ የጦር ወጪያቸውን እንዲያሳድጉ ቀደም ሲል ውሳኔ ላይ ደርሷል፡፡


የጀርመንም የሰራዊት አባላት ማብዛት እና የጦር አቅምን ማደርጀት የዚሁ ውሳኔ አካል ነው ተብሏል፡፡


ኔቶ በአሁኑ ወቅት ከሩሲያ ጋር በቋሚ የጦር ፍጥጫ ላይ እንደሚገኝ ይነገራል፡፡

ree

በሱዳን የኮሌራ ወረርሽኙ እየተባባሰ ነው ተባለ፡፡

የአለም የጤና ድርጅት በሱዳን የኮሌራ ወረርሽኝ መዛመት በእጅጉ ከአሳሳቢው ደረጃ ላይ ደርሷል ማለቱን አናዶሉ ፅፏል፡፡


ወረርሽኙ ከአመት በፊት አንስቶ በአገሪቱ በስፋት እየተዛመተ ነው ተብሏል፡፡


በዚህ ጊዜ በኮሌራ በሽታ የታመሙ ሰዎች ብዛት ከ113 ሺህ 600 በላይ መድረሱ ተጠቅሷል፡፡

ከ3 ሺህ የሚልቁ ሰዎች በበሽታው ሕይወታቸው ማለፉን የአለም የጤና ድርጅት መረጃ ያሳያል፡፡


ሱዳን ከ2 አመታት በላይ በመንግስት ጦር እና በRSF ፈጥኖ ደራሽ ሀይል መካከል በሚካሄድ ውጊያ በጦርነት ላይ መሆኗ ይታወቃል፡፡

ጦርነቱ የአገሪቱን ወረርሽኝ የመከላከል አቅም በእጅጉ እያዳከመው መሆኑ ይነገራል፡፡

ree

በማላዊ በቅርቡ በተካሄደው ምርጫ የቀድሞው ፕሬዘዳንት ፒተር ሙታሪካ እየመሩ ነው ተባለ፡፡


ሙታሪካ ለፕሬዘዳንታዊ ፉክክሩ ከተሰጠው ድምፅ 66 በመቶውን ማግኘታቸውን የቅድሚያ ውጤቶች እንደሚያሳዩ ቢቢሲ ፅፏል፡፡


ፒተር ሙታሪካ የፕሬዘዳንት ላዛርስ ቻክዌራ የድጋፍ መሰረት የሰፋባቸው ናቸው በተባሉ ግዛቶች ሳይቀር ማሸነፋቸው ተጠቅሷል፡፡


ፕሬዘዳንት ላዛርስ ቻክዌራ እስካሁን ያገኙ የተረጋገጠ የድምፅ ውጤት ከ24 በመቶ ያልበለጠ ነው ተብሏል፡፡


የምርጫ ኮሚሽኑ የተጠቃለለ ውጤቱን ዛሬ ይፋ እንደሚያደርግ ተጠቅሷል፡፡


ኮሚሽኑ ውጤቱንም ግልፅ ፣ ትክክለኛ እና ተአማኒ አደርጋለሁ ማለቱ ተሰምቷል፡፡


የኔነህ ከበደ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page