top of page

ሐምሌ 9፣ 2016 - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከመደራጀቱ በፊት በለያቸው አምስት መሰረታዊ ነጥቦችን ዙሪያ እየሰራ ነው ተባለ

  • Jul 16, 2024
  • 1 min read

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከመደራጀቱ በፊት በለያቸው አምስት መሰረታዊ ነጥቦችን ዙሪያ እየሰራ ነው ተባለ፡፡


በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብርናና የገጠር ልማት ክላተር አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር ለሸገር እንደተናገሩት የክልሉ ሀብት ሰው መሆኑን በማስቀደም ክልሉ ከመደራጀቱ በፊት ትኩረት ከሰጠባቸው ነጥብ ውስጥ አንዱ ነው፤ የአካባቢው የሰላም ሁኔታም ሌላኛው ነው ብለዋል፡፡


የግብርና ምርትን በማሳደግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከውጪ የሚገቡ የምግብ እህሎችንና ሰብሎችን በክልሉ ማምረትና መተካት ሌላው ጉዳይ መሆኑን ምክትል ርዕስ መስተዳድሩ ነግረውናል፡፡


የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎችን በገጠር ማስፋፋትም ቀደም ሲል ክልሉ ከመደራጀቱ በፊት ከተለዩ ነጥቦች ማዕከል እንደሚገኙበትም ተሰምቷል፡፡



Recent Posts

See All
በኢትዮጵያ የንግዱን ማህበረሰብ እየገጠሙ ካሉ ችግሮች 40 በመቶ ያህሉ ከገንዘብ አቅርቦት ጋር የተገናኙ ናቸው ተባለ ።

መጋቢት 3/2018 በኢትዮጵያ የንግዱን ማህበረሰብ እየገጠሙ ካሉ ችግሮች 40 በመቶ ያህሉ ከገንዘብ አቅርቦት ጋር የተገናኙ ናቸው ተባለ ። በአጠቃላይ በኢትዮጵያ 2 ሚሊየን የሚጠጉ ጥቃቅን ፣ አነስተኛና መካከለኛ የንግድ ኢንዱስትሪ ተቋማት እንዳሉ ተነግሯል። የእነዚህ ኢንዱስትሪ ባለቤቶችና ኢ-መደበኛ በሆኑ ሌሎች ንግ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page