top of page

ሐምሌ 5 2017 - ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ “ንብ ተራ ኦንላይን“ የተሰኘ መተግበሪያ ወደ ስራ አስገባ።

  • sheger1021fm
  • Jul 12
  • 1 min read

መተግበሪያው ደንበኞች ግብይቶችንና ክፍያዎችን በቀላሉ ስልካቸውን በመጠቀም ለመፈጸም የሚያስችላቸው መሆኑን ሰምተናል።


ንብ ተራ ኦንላይን በርካታ አገልግሎቶችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማከናወን የሚያስችል መተግበሪያ ነው ተብሏል።


ተቋማት የበጀት አስተዳደራቸዉን በተሻለ መንገድ እንዲመሩበት፤ ከባንክ ወደ ባንከ የሚተላለፉ ክፍያዎችን እንዲፈፅሙበት እና ሌሎች የባንከ ሥራዎችን ያቀልላቸዋል መባሉን ሰምተናል።


መተግበሪያውን ባንኩ በራሱ ልጆች እንዳበጀው ተነግሯል።


የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሔኖክ ከበደ ንብ ባንክ ወደ ሥራ ያስገባው ይህ መተግበሪያ ጊዜውን የዋጀ እና የባንክ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ለደንበኞቹ የተመቸ አገልግሎሎቶችን የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል።


አቶ ሔኖክ ጨምረውም ይህ ሱፕርአፕ ለደንበኞች የተሟላ፤ ምቹ፣ ቀላልና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መተግበሪያ ነው ብለዋል።

ree

ባንኩ አዲስ የሦስት ዓመት ስትራቴጂ ዕቅድና የአምስት ዓመት ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀቱን ተናግሯል።


በሁሉም መመዘኛዎችም ንብ ባንክ የነበሩ ጉድለቶችን በማረም የተሻለ አፈፃፀም እንዲኖረው ይህ ስትራቴጂ ያግዘዋል ተብሏል።


ንብ ተራ ሱፐር አፕ መተግበሪያ ለዚህ እቅድ መሳካት አንደኛው መንገድ ነው ተብሎለታል።


ይህ የ3 ዓመት ስትራቴጂ ዕቅድ ከባንኩ ቦርድ ጀምሮ በየደረጃው የሚገኙ የባንኩ ሠራተኞች ጋር ተመክሮበታል ተብሏል።


አዲሱ የንብ ባንክ ስትራቴጂ እቅድ ቀደም ሲል የነበሩ ጉድለቶችን በማረም ባንኩን ወደፊት የሚያራምዱና የሚያሳድጉ ሥራዎች እንደሚሰሩበት ተስፋ ተጥሎበታል።


ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
ጥቅምት 20 2018 - የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ

የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳቦች ያለ በቂ ምክንያት የማይፈፅሙ ተቋማት በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ቢሞክርም ባለው የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡ ተቋሙ የአስተዳደር በደል ደረሰብን እምባችን ይታበስልን የሚሉ አቤት ባዮችን ቅሬታ በመቀበል

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page