ሐምሌ 4 2017 - የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ የሩሲያ መገበያያ ገንዘብ ሩብል፤ ከኢትዮጵያ ብር ጋር ያለውን የምንዛሪ ተመን ይፋ አደረገ፡፡
- sheger1021fm
- 5 days ago
- 1 min read
100 የኢትዮጵያ ብር በ57.5872 የሩሲያ ሩብል እንዲመነዘር ተመን ወጥቶለታል፡፡
የሁለቱ ሀገራት ገንዘቦች የእርስ በእርስ የምንዛሪ ተመን መቀመጡ በመካከላቸው ያለውን የንግድና ሌላውንም ልውውጦች በቀጥታ ለማከናወን እንዲችሉ ያደርጋቸዋል ተብሏል፡፡
የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ የኢትዮጵያ ብር የምንዛሪ ተመን ይፋ ሲያደርግ ለኢትዮጵያ ብር ኮድ 230 የመለያ ቁጥር ሰጥቷል፡፡
ከዚህ በኋላም የኢትዮጵያ ብር ከሩሲያ ሩብል ያለው የምንዛሪ ተመን በየጊዜው ማሻሻያ እየተደረገበት ይቀጥላል ተብሏል፡፡

የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ከዶላር ተፅዕኖ ነፃ ሆኖ ከሀገራት ጋር ያለውን የንግድና ሌላውንም ግንኙነት ለማቀላጠፍ ኢትዮጵያን ጨምሮ የ12 ሀገራትን ገንዘብ ነው የምንዛሪ ተመን እንዲወጣላቸው ያደረገው ተብሏል፡፡
ከኢትዮጵያ በተጨማሪ የተካተቱት የባንግላዴሽ፣ የባህሬን፣ የቦሊቪያ፣ የኩባ፣ የአልጀርያ፣ የኢራን፣ የማያንማር፣ የሞንጎሊያ፣ የናይጀርያ፣ የኦማን እና የሳውዲ አረቢያ ገንዘቦች መሆናቸው ተነግሯል፡፡
ቴዎድሮስ ወርቁ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
Comments