ሐምሌ 29 2017 -በኦሞ ወንዝ ሙላት ምክንያት ከአምስት ዓመት በፊት የተፈናቀሉ ሰዎች አሁንም በመጠለያ ውስጥ ናቸው ተባለ
- sheger1021fm
- Aug 5
- 1 min read
በኦሞ ወንዝ ሙላት ምክንያት ከአምስት ዓመት በፊት የተፈናቀሉ ሰዎች አሁንም በመጠለያ ውስጥ ናቸው ተባለ፡፡
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ደቡብ ኦሞ ዞን #ዳሰነች ወረዳ በ2012 ዓ.ም በኦሞ ወንዝ ሙላት ምክንያት የተፈናቀሉ ሰዎች 79,000 እንደሚደርስ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ተናግሯል፡፡
ኮሚሽኑ በዓመታዊ ሪፖርቱ ይፋ እንዳደረገው ተፈናቃዮቹ ሪፖርቱ እስከተጠቃለለበት ያለፈው ሰኔ ወር ድረስ በ12 መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ይገኛሉ፡፡
በአፋር፣ በአማራ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያና ትግራይን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎችም የሃገር ውስጥ ተፈናቃዮች መኖራቸውን የጠቀሰው ኢሰመኮ በቂ ሰብአዊ ድጋፍ እየቀረበላቸው እንዳልሆነ ጠቅሷል፡፡
ዘላቂ መፍትሄም ሳያገኙ ፍላጎታቸውን በበቂ ሁኔታ በሚያሟላ ሰብአዊ ድጋፍ ላይ ጥገኛ ሆነው ለተራዘመ የመፈናቀል ሁኔታ ውስጥ መቆየታቸውም አሳሳቢ ነው ብሏል፡፡
ኮሚሽኑ በጎርፍ የተፈናቀሉ ብሎ ከጠቀሳቸው 79 ሺህ የዳሰነች ወረዳ ተፈናቃዮች ውጭ በሌሎች አካባቢዎች ያሉ የሃገር ውስጥ ተፈናቃዮችን ቁጥርና ያሉበትን ሁኔታ ግን በዝርዝር በሪፖርቱ አልካተተም፡፡
ትዕግስት ዘሪሁን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyu.com/ycxjmm3s












Comments