top of page

ሐምሌ 25፣2016 - ለዋጋ ንረት ያጋልጣል የተባለው ፉክክር ማብቂያው መቼ ይሆን? የሚያስከትለውስ አሉታዊ ተፅዕኖስ

  • sheger1021fm
  • Aug 1, 2024
  • 1 min read

የውጭ ምንዛሪ ተመኑ ከብሔራዊ ባንክ እጅ ወጥቶ ገበያ መር ከሆነ በኋላ በሰዓታት ልዩነት ውስጥ የብር የመግዛት አቅም እየተዳከመ ነው፡፡


ባንኮችም የውጭ ሀገር ገንዘቦችን የሚገዙበትን ዋጋ በሰዓታት ልዩነት ጭምር ከፍ በማድረግ ፉክክራቸውን ቀጥለዋል፡፡


እንዲህ ያለውና ለዋጋ ንረት ያጋልጣል የተባለው ፉክክር ማብቂያው መቼ ይሆን? የሚያስከትለውስ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚሉና ሌሎች ጉዳዮች ላይ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ጠይቀናል፡፡


ያነጋገርናቸው የምጣኔ ሐብት ባለሙያ ዋሲሁን በላይ ባለሞያ እንደሚሉት..

• ባንኮች የውጭ ምንዛሬ መግዣ ዋጋቸውን በሰዓት ልዩነት ከፍ እያደረጉ የሚፎካከሩት ያለችውን ውስን የውጭ ምንዛሬ ለመሰብሰብ ካላቸው ፍላጎት የተነሳ ነው፡፡


• የመግዣ ዋጋው በየጊዜው ከፍ እያለም ጣሪያው የት እንደሚደረስ ለመገመት በሚያስችግር ሁኔታ መቀጠሉ አይቀሬ ነው፡፡ እኛም እየሄድንበት ያለው መንገድ ተመሳሳይ ነው፡፡


• ናይጀሪያ አምና በIMF ምክረ ተመሳሳይ ፖለሲ ተግባራዊ አድርጋ ዘንድሮ አንድን ዶላር በ1 ሺህ 480 ናይራ እየመነዘረች ነው፡፡


• የምንዛሬ ዋጋው ተመን ከፍ ባለ ቁጥር እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ከፍተኛ የገቢ ምርት ከውጭ ለሚያስመጡ ሃገራት የዋጋ ንረቱን ጫና እያከፋው ይሄዳል፡፡


• በተለይ ቋሚ ደመወዝ የሚያገኘው በዋጋ ንረቱ ከፍተኛ ፈተና ውስጥ ሊገባ ይችላል፡፡


• የጥቁር ገበያውን ተወዳዳሪ እስከማይሆንበት ደረጃ ለማድረስ እና ባንኮች በቂ የውጭ ምንዛሪ ክምችት እስኪኖራቸው ድረስ የባንኮች የውጭ ምንዛሬ የመግዣ ጣሪያ ከፍ እያለ ይቀጥላል፡፡


• በቅርቡ በቂ ክምችት ይኖራል ወይ? ጥቁር ገበያውስ ይጠፋል ወይ? የሚለው ግን አጠያያቂ ነው፡፡

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page