top of page

ሐምሌ 24፣2016 - የፍልስጤሙ የጦር ድርጅት ሃማስ የፖለቲካ መሪ ኢስማኤል ሃኒያ ኢራን ውስጥ በአየር ጥቃት መገደላቸው ተነገረ

  • Jul 31, 2024
  • 1 min read

የፍልስጤሙ የጦር ድርጅት ሃማስ የፖለቲካ መሪ ኢስማኤል ሃኒያ ኢራን ውስጥ በአየር ጥቃት መገደላቸው ተነገረ።


ሃኒያ በኢራን ዋና ከተማ ቴሄራን ባለ መኖሪያ ቤታቸው የተገደሉት በእስራኤል የአየር ጥቃት ነው ሲል ሃማስ ከሷል።


ሃኒያ በቴሄራን የተገኙት በአዲሱ የኢራን ፕሬዝዳንት ማሱድ ኤዝሽኪያን በዓለ ሲመት ላይ ለመታደም እንደነበር ተነግሯል።


አንድ ጠባቂያቸውም አብሮ መገደሉ ታውቋል። ሃማስ ለግድያው እስራኤልን ተጠያቂ አድርጓል።


ኢራን በበኩሏ በግድያው ዙሪያ ማጣራት እያካሃድኩ ነው ብላለች።


እስራኤል ግን ስለ ግድያው እስከ አሁን ያለችው ነገር የለም።

ከዚህ ቀደም ግን ለጥቅምት ሰባቱ ጥቃት በቀል ሃኒያን እና ሌሎች የሃማስ መሪዎችን ለመግደል ስትዝት እንደቆየች አሶሼትድ ፕሬስ አስታውሷል።


ሃማስ ለግድያው እስራኤልን እንደሚበቀል ዝቷል።


የኢራን የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቀባይም የሃማሱ መሪ ደም ፈሶ አይቀርም ብሏል።


መቀመጫውን በዌስት ባንክ ያደረገው የፍልስጤም አስተዳደር ፕሬዝዳንት ማህሙድ አባስ ደግሞ የሃኒያን ግድያ አውገዘዋል።


ንጋቱ ረጋሳ


Recent Posts

See All
የሐምሌ 23 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ግብፅ በግብፅ የሜዴትራኒያን የባህር ዳርቻ የነበረ የአሜሪካ የጋዝ ማጠራቀሚያ መርከብ በድሮን ተመታ ተባለ፡፡ ሁለት የደህንነት ምንጮች መርከቡ በድሮን እንደተመታ አረጋግጠውልኛል ሲል ሬውተርስ ፅፏል፡፡ መርከቡ በድሮን እንደተመታ በእሳት መያያዙ ታውቋል፡፡ ቃጠሎው ወደ ሌላ መርከብም ተጋብቶ ነበር ተብሏል፡፡ ኋላ ግን

 
 
 
የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ማሳደግ፣አፍሪካዊያን የጋራ መጪ እድላቸውን እንዲቀርፁ ማገዝ ያስፈልጋል ተባለ።

ሐምሌ 23 2018 የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ማሳደግ፣አፍሪካዊያን የጋራ መጪ እድላቸውን እንዲቀርፁ ማገዝ ያስፈልጋል ተባለ። የአፍሪካ ሀገሮች እርስ በእርስ፣በአፍሪካና በሩሲያ እንዲሁም አፍሪካ ከተቀረው ዓለም ጋር ያላትን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ማሳደግን ዓለማው ያደረገ ዓለም አቀፍ ጉባኤ በተባበሩት መንግስታት የአ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page