ሐምሌ 23 2017 - የምክክር ኮሚሽንን ተልዕኮና ዓላማ ተረድተው አብረውት እየሰሩ ያሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጥቂቶች ብቻ ናቸው ተባለ
- sheger1021fm
- Jul 30
- 1 min read
በኢትዮጵያ ካሉ ወደ 5,000 ገደማ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ውስጥ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን ተልዕኮና ዓላማ ተረድተው አብረውት እየሰሩ ያሉት ጥቂቶች ብቻ ናቸው ተባለ፡፡
ይህን ያለው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ነው፡፡
ምክር ቤቱም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የኮሚሽኑን ዓላማ ካለመረዳትና በፋይናንስ እጥረት ምክንያት በሚፈለገው ልክ በአገራዊ ምክክሩ ላይ እየተሳተፉ እንዳልሆነ አስረድተዋል፡፡
በምክሩ ላይ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሚፈለገው ደረጃ በንቃት አለመሳተፍ እንደሚያሳስበው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ተናግሯል፡፡
ድርጅቶቹ በምክሩ ላይ እንዲሳተፉ ማህበረሰቡንም እንዲያነቁ አለም የገንዘብ ለጋሽ ድርጅቶች ድጋፍ እያደረጉ እንዳልሆነ ምክር ቤቱ ጠቁሟል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..
ያሬድ እንዳሻው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s












Comments