top of page

ሐምሌ 22 2017 - የውጭ ምንዛሪ በገበያው እንዲወሰን ያስቻለ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ከተደረገ ዓመት ሆነው፡፡

  • sheger1021fm
  • Jul 29
  • 1 min read

ሪፎርሙ የብሔራዊ ባንክ የመጠባበቂያ ክምችትን ማሳደጉ፣ በወጪ ንግድ በመሳሰሉት ከፍተኛ ውጤት እንዲመጣ ማስቻሉ ተነግሯል፡፡


ለንግድ፣ ለትምህርት፣ ለጉብኝት ወደ ውጪ ሀገር የሚሄዱ ሰዎችም ማሻሻያው ከተደረገ በኋላ በተሻለ መጠን ዶላር እየቀረበላቸው መሆኑም ይሰማል፡፡፡


ግን ባንኮች ዶላር ለጠየቃቸው እስከ 200 በመቶ ተቀማጭ እየጠየቁ ነው የሚል ክስ ቀርቧል፡፡


ማዕከላዊ ባንኩ በቂ የውጪ ምንዛሪ እና መደላድል አለ ቢልም ባንኮች ግን በምትኩ የውጭ ምንዛሪ ለመስጠት እስከ 200% ተቀማጭ እየጠየቁ ነው ፤ ቢውሮክራሲም እያበዙ ነው ተብሏል።


ብሔራዊ ባንክም ይህንን የሚያደርጉትን ጠቁሙኝ ብሏል፡፡ ባለሞያዎችስ ምን ይላሉ?


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….


ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page