top of page

ሐምሌ 22 2017 - አለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው አተገባበር ላይ ስጋት አለኝ ብሏል

  • sheger1021fm
  • Jul 29
  • 1 min read

የፀጥታ ችግሮች እልባት አለማግኘታቸው፣ በጥቁር ገበያውና በመደበኛው የምንዛሪ ዋጋ መካከል ልዩነቱ እየሰፋ መሄዱ፣ የታሰበውን ያህል የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት አለመገኘቱ፣ እርዳታና ድጋፎች መቀነሳቸውና ሌላውንም በማንሳት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ወደ ኋላ ሊያንሸራትተው ይችላል ብሏል፡፡


ኢትዮጵያ ከIMF ጋር ለ4 ዓመት ውል አስራ እየተገበረችው ባለው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተቋሙ ከሳምንት በፊት ያወጣው ሪፖርት ለሶስተኛ ጊዜ ግምገማ ካደረገ በኋላ ይፋ ያደረገው ነው፡፡


በዚህም ለመጀመሪያ ጊዜ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ወደ ኋላ ሊወስዱ ይችላሉ ያላቸውን ስጋቶችን በዝርዝር አሳውቋል፡፡


በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው የፕራግማ ካፒታል ስራ አስፈፃሚ እና የኢንቨስትመንትና ፋይናንስ ባለሙያው መርዕድ ፍቅረዮሐንስ በተቋሙ የተነሱት ስጋቶች ትክክል መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ree

የገንዘብ ሚኒስቴር በመጭው ነሐሴ ወር ከ44 አባዳሪዎች ጋር ድርድር እንደሚጠብቀው ጠቅሰው IMF ሶስተኛ ያወጣውን ይሄንኑ ሪፖርት በጥብቅ እንደሚከተሉት የሚጠረጠር አይደለም ብለዋል፡፡


በመሆኑም በድርድሩም ወቅት ሊነሳ የሚችለው ዋናው ጉዳይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ይሳካል ወይ? የሚለው እንደሚሆን ጠቅሰው ኢትዮጵያ ለህልውናዋ ስትል የጀመረችውን ማሻሻያ እንዲሳካና ማስተካከያ የሚያስፈልጋቸውን የቤት ስራዎች ሁሉ በመስራት በትክክለኛው ሐዲድ እንዲሄድ ማድረግ ይጠበቅባታል ሲሉ አሳስበዋል፡፡


ውል ገብታ ብድር የወሰደችበት ማሻሻያ ካልተሳካና ወደኋላ ከሄደ ለኢትዮጵያ እጅግ የከፋ ይሆናልም ይላሉ፡፡


ካልተሳካላት የፋይናንስ አበዳሪና ደጋፊዎች በጥርጣሬ የሚያዩዋት፣ ትሆናለች ተብሏል፡፡


ለምታቅዳቸው ፕሮጀክቶችም ፋይናንስ ድጋፍ ማግኘት የሚቸግራትና ለኢኮኖሚዋም ወደ መደበኛ አሰራር ያስገባቻቸው አሰራሮች ሁሉ ከእጇ የሚያመልጡ እንደሚሆን ስጋታቸውን ተናግረዋል፡፡


IMF በጠንካራ ጎን የጠቀሳቸው ነጥቦችም አሉ፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….


ትዕግስት ዘሪሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page