ሐምሌ 19 2017 - የጎንደሯ ነዋሪ የሽቱ ምስጋናው በኢትዮጵያ ሎተሪ ታሪክ ከፍተኛ የሆነውን 50 ሚሊዮን ብር ሎተሪ አሸናፊ ሆነች
- sheger1021fm
- Jul 26
- 1 min read
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት የሚሊዮን ሎተሪ እና የቶምቦላ እጣ ባለዕድለኞችን በዛሬው እለት ሸልሟል።
ብሔራዊ ሎተሪ ያዘጋጀው የ50 ሚሊዮ ብር ሎተሪ እጣ ግንቦት 30/2017 ዓ.ም መውጣቱ ይታወሳል፡፡
በተመሳሳይ የቤት እና የመኪና ዕጣዎችም ከተጨማሪ የገንዘብ ሽልማት ጋር ያቀረበው ቶምቦላ ሎተሪ ባለፈው ሰኔ 29 አሸናፊዎቹ ይፋ ማድርጉ ይታወቃል፡፡

በዚህም የ50 ሚሊዮን ሎተሪ እና የቶምቦላ ሎተሪ አሸናፊወች ሽልማታቸውን ዛሬ ተረክበዋል፡፡
የሚሊዮን ሎተሪ ዕድለኞች የአንደኛ እጣ አሸናፊ የሆነችው የሽቱ ምስጋናው ከጎንደር 50 ሚሊዮን ብር አሸናፊ ሆናለች፣ ሽልማቷንም ተቀብላለች።
ካሳ አለሙ አባይ የተባሉ ከትግራይ ነዋሪ ደግሞ 25 ሚሊዮን አሸናፊ ሆነዋል፣ ሽልማታቸውንም ተቀብለዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ በቶምቦላ ሎተሪ ነጋልኝ አበራ ብሩ ከኦሮሚያ ም/ሸዋ 1ኛ ዕጣ ባለ 3 መኝታ መኖሪያ ቤት ከተጨማሪ ለ3 ዓመት 60ሺህ አሸናፊ ሆነዋል።
ሌሎችም አሸናፊዎች ሽልማቶቻቸውን ዛሬ ተቀብለዋል።
ፍቅሩ አምባቸው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s












Comments