top of page

ሐምሌ 17 2017 - ብርሃንን የመለየት ችግርን ለማስተካከል ያለመ የዓይን ቀዶ ህክምና ማዕከል በኢትዮጵያ ስራ ጀመረ

  • sheger1021fm
  • Jul 24
  • 1 min read

በኢትዮጵያ የአይን ህክምና ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያው ነው የተባለለት ብርሃንን የመለየት ችግርን ለማስተካከል ያለመ የዓይን ቀዶ ህክምና ( #Refractive_Surgery ) ማዕከል ስራ ጀመረ።


ማዕከሉን የከፈተው ብሩህ ቪዥን ልዩ የአይን ህክምና ማዕከል ነው፡፡


ሪፍራክቲቭ ሰርጀሪ የተሰኘው ይህ የዓይን ሕክምና ከሩቅና ከቅርብ ማየት አለመቻልን እንዲሁም መሰል የዕይታ ችግሮችን ለማስተካከል ያለመ የዓይን ቀዶ ህክምና ዓይነት መሆን ሲነገር ሰምተናል፡፡


በኢትዮጵያ የዓይን ህክምና የሚሰጡ የህክምና ተቋማት ጥቂት በመሆናቸው ታክመው ሊድኑ የሚችሉ የአይን ህመሞች በጊዜ መታከም እየቻሉ እንዳልሆነ የተነገረ ሲሆን ትናንት ስራውን የጀመረው ሪፍራክቲቭ ሰርጀሪ ማዕከል ያለው ችግር ያቃልላል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበታል።

ree

ቀዶ ህክምናው ከ8 እስከ 10 ደቂቃዎች ብቻ ነው የሚከወነው የተባለ ሲሆን በተጨማሪም ለዚህ ህክምና ወደ በውጭ ሀገራት የሚደረግን የህክምና ጉዞ ያስቀራል ተብሏል።


በኢትዮጵያ የአይን ህክምና ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያው ነው የተባለለት ብርሃንን የመለየት ችግርን ለማስተካከል ያለመ የዓይን ቀዶ ጥገና ማዕከል (ሪፍራክቲቭ ሰርጀሪ ማእከል) አገልግሎቱን ወሎ ሠፈር ቢራ ሕንጻ በሚገኘው ብሩህ ቪዥን ልዩ የአይን ህክምና ማዕከል እንደሚሠጥ ተነግሯል፡፡


ፋሲካ ሙሉወርቅ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page