top of page

ሐምሌ 17 2017 - በደቡብ ምዕራብ ህዝቦች ክልል የመሬት መንሸራተት ቤቶችን እያፈራረሰ፣ ሰዎችን እያፈናቀለ መሆኑ ተሰማ

  • sheger1021fm
  • Jul 24
  • 1 min read

በደቡብ ምዕራብ ህዝቦች ክልል የመሬት መንሸራተት ቤቶችን እያፈራረሰ፣ ሰዎችን እያፈናቀለ መሆኑ ተሰማ፡፡

ከፋ፣ ቤንች ሸኮ ችግሩ ከደረሰባቸው የክልሉ ዞኖች መካከል ሲሆኑ የመሬት መንሸራተት ስጋት ያለባቸው ሌሎች አካባቢዎችም አሉ ተብሏል፡፡


ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በ20 ቀበሌዎች ላይ የመሬት መንሸራተት አደጋ መድረሱ ተነገረ፡፡


በክልሉ 80 መኖሪያ ቤቶች መውደማቸው በ23.7 ሄክታር መሬት ላይ ያለሰብል ላይም ጉዳት መድረሱ ተነግሯል፡፡


በሌሎች 30 ወረዳዎች ላይም ስጋት መሆኑንና በዚህም 49 አባወራዎች ከቤት ንብረታቸው እንደተፈናቀሉ ከክልሉ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ሰምተናል፡፡

ree

ከፋ፣ ቤንች ሸኮ ችግሩ ከደረሰባቸው የክልሉ ዞኖች መካከል ናቸው፡፡ የቤት እንስሳትም ሞተዋል ተብሏል፡፡


በአጠቃላይ በክልሉ ከ200 በላይ ሰዎች በጉዳትና በስጋት ከአካባቢያቸው እንዲወጡ መደረጉን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት ለማ መለሰ ነግረውን፡፡


አሁን ላይ የሰብዓዊ ድጋፍ የሚፈልጉትን በመለየት ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን እና ስጋት ያለባቸው አካባቢዎች ላይ ደግሞ የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተሰራ መሆኑን ከኮሚሽኑ ሰምተናል፡፡


አሁንም የዝናቡ ሁኔታ አሳሳቢ በመሆኑ ጥንቃቄ የሚፈልግ ነው ተብሏል፡፡


ማርታ በቀለ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
ታህሳስ 3/2018 የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሃይል ፍጆታ ካለፈው ሃምሌ ወር ወዲህ እያደገ መጥቷል ተባለ።

ኢትዮጵያ ከተለያዩ ምንጮች ከምታመርተው የኤሌክትሪክ ሃይል 90 በመቶው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል እንደሆነ ተጠቅሷል። በዘንድሮው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አራት ወራት ኢትዮጵያ ከውሃ እና ከነፋስ ከ15,300 ጊጋዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨቷ ተነግሯል። በየወሩ በአማካይ 3,800 ጊጋዋት ሰአት የኤ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page