ሐምሌ 12 2017 - ''ኪን ኢትዮጵያ'' የተባለ የኪነ ጥበብ ጉዞ በተለያዩ የአለም ክፍሎች ሊዘዋወር ነው ተባለ
- sheger1021fm
- Jul 19
- 1 min read
70 አባላት ያሉት የኪነ-ጥበብ ቡድን የኢትዮጵያ ቱሪዝም፣ የኢንቨስትመንት አማራጭና ሌሎች ሀብቶቿን ለማስተዋወቅ በማሰብ ''ኪን ኢትዮጵያ'' የተባለ የኪነ ጥበብ ጉዞ በተለያዩ የአለም ክፍሎች ሊዘዋወር ነው ተባለ፡፡
ጉዞው ሐምሌ 13 የሚጀምር ሲሆን ከተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች የተውጣጡ የኪነ ጥበብ ባለሞያዎችን በዚህ የኪነ ጥበብ ጉዞ ላይ እንደሚሳተፉ ተነግሯል።
ጉዞውን በበላይነት ያሰናዱት የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት፣ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴርና ሻኩራ ስቱዲዮ በጋራ በመሆን ነው ሲሉ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁ ጎበዛይ ተናግረዋል።
መንግስት ቅድሚያ በመዳረሻ ሀገራት ላይ አስፈላጊው ግንኙነትና ዝግጅቶች አድርጓል ሲሉም አክለዋል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ነብዩ ባዬ በበኩላቸው ከ39 ዓመት በፊት ህዝብ ለህዝብ በሚል በተመሳሳይ መንገድ የኪነ -ጥበብ ባለሙያዎች ጉዞ በተለያዩ ሃገራት አድርገው የነበረ አሁን የሚደረገው ጉዞ የኢትዮጵያ መንግስት ከመዳረሻ ሃገራት መንግስታት ጋር ቅድሚያ በጉዳዩ ላይ ኦፊሴሊያዊ ግንኙነት ማድረጉን ተናግረዋል።
ባለሙያዎቹ ኢትዮጵያ በኪነ ጥበቡ ዘርፍ ያላትን ሀብት በሚገባ ያስተዋውቃሉ ሲሉም ጠቅሰዋል።
ኪን ኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ጉዞ ኢትዮጵያ በቱሪዝም ያላትን ሃብት መንገርና ሃገሪቱ ያላት የኢንቨስትመንት አማራጭ ለአለም ሃገራት ለማስተዋወቅ ያለመ ነው ተብሏል።
አርቲስት ካሙዙ ካሳ የኪነ ጥበብ ጉዞው የመጀመሪያው የፊታችን እሁድ ወደ ቻይና በማምራት ነው ያለ ሲሆን በቻይና በሁለት ከተሞች ስራዎቹን ያቀርባል ብሏል።
ባለፉት 3 ወራት የኪነ-ጥበብ ቡድኑ ልምምድን ሲያደርግ ነበር ከሙዚቃ ስራ ባለፈም የፋሽን ትርኢትና ሌሎች ስራዎች ይቀርባሉ ሲል ተናግሯል።
የቻይናው ጉዞ ሲጠናቀቅ ቀጣይ ሃገራት ይፋ ይደረጋሉ ተብሏል።
በረከት አካሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s












Comments