ለመጪውን የፈረንጆች አዲስ ዓመት እንዲሁም የገና በዓል ወደ ቤተሰቦቻቸው ለሚሄዱ የውጪ ዜጎች አውደርዕይ መሰናዳቱ ተነገረ
- sheger1021fm
- Nov 21
- 1 min read
ህዳር 12 2018
መጪውን የፈረንጆች አዲስ ዓመት እንዲሁም የገና በዓል አስመልክቶ ወደ ቤተሰቦቻቸው ለሚሄዱ የውጪ ሃገር ዜጎች በተለይም ለዲኘሎማቲክ ማህበረሰቡ አውደርዕይ መሰናዳቱ ተነገረ፡፡
ኢትዮጵያን ለዓለም ሀገራት ለማስተዋቅ የተለያዩ ለስጦታ የሚሆኑ ምርቶች ይገኙበታል የተባለው አውደርዕይ የተሰናዳው በሦስት ድርጅቶች ነው ተብሏል፡፡
ኤልቬዜት ኢንተርናሽናል ኤቨንት፣ ዲሊኦፖል ሆቴል፣ እና ሳራ ኔክስት ፋሽን ዲዛይን በጋራ አውደርዕዩን ማሰናዳታቸው ተነግሯል፡፡
የፈረንጆቹ የገና በዓል የተለያዩ ስጦታዎች የሚሰጡበት በመሆኑ ይህንን እድል በመጠቀም ምርቶች እንዲተዋወቁ አውደ ርዕዩ መሰናዳቱን የሳራ ኔክስት ፋሽን ዲዛይን መስራች ሳራ መሀመድ ተናግረዋል፡፡

በአውደ ርዕዩ በተለያዩ ምርቶች ንግድ ላይ የተሰማሩ ሴቶች እንደሚሳተፉ እና ልምድ የሚለዋወጡበትም እንደሚሆን ይጠበቃል ብለዋል፡፡
ይህንንም በመጠቀም ምርቶቻቸውን የሚያስተዋውቁ አምራቾች በገበያ ላይ ያላቸውን ተወዳዳሪነት ለመጨመርና የተሻለ የገበያ እድል እንዲፈጠርላቸውም ያግዛል ተብሏል፡፡
የኤልቬዜት ኢንተርናሽናል ኤቨንት ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ሩት ኃይሉ በበኩላቸው የተዘጋጀው አውደ ርዕይ ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ መሆኑንና በዓይነቱ ለየት ባለ መልኩ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ላይ በማተኮር የተለያዩ ዝግጅቶች የተሰናዱበት ነው ብለዋል፡፡
ዲፕሎማቶች የተለያዩ ኤምባሲ ተወካዮች የንግድ ተቋማት መሪዎች እና በተለያየ ሙያ ላይ ያሉ እንግዶች ይገኛሉ ተብሎም ይጠበቃል ብለዋል፡፡
በሦስቱ ተቋማት የተሰናዳው የዲፕሎማቲክ አውደ ርዕይ ከመጪው ህዳር 19-21 2018 ዓ.ም በዲሊኦፖል ሆቴል የሚካሄድ ሲሆን ኢትዮጵያን የሚያስተዋውቁ የተለያዩ ምርቶች የሚቀርቡበት እንደሆነም ሰምተናል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….
ምህረት ስዩም
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s











Comments