top of page

ለመጪውን የፈረንጆች አዲስ ዓመት እንዲሁም የገና በዓል ወደ ቤተሰቦቻቸው ለሚሄዱ የውጪ ዜጎች አውደርዕይ መሰናዳቱ ተነገረ

  • sheger1021fm
  • Nov 21
  • 1 min read

ህዳር 12 2018

 

መጪውን የፈረንጆች አዲስ ዓመት እንዲሁም የገና በዓል አስመልክቶ ወደ ቤተሰቦቻቸው ለሚሄዱ የውጪ ሃገር ዜጎች በተለይም ለዲኘሎማቲክ ማህበረሰቡ አውደርዕይ መሰናዳቱ ተነገረ፡፡

 

ኢትዮጵያን ለዓለም ሀገራት ለማስተዋቅ የተለያዩ ለስጦታ የሚሆኑ ምርቶች ይገኙበታል የተባለው አውደርዕይ የተሰናዳው በሦስት ድርጅቶች ነው ተብሏል፡፡

 

ኤልቬዜት ኢንተርናሽናል ኤቨንት፣ ዲሊኦፖል ሆቴል፣ እና ሳራ ኔክስት ፋሽን ዲዛይን በጋራ አውደርዕዩን ማሰናዳታቸው ተነግሯል፡፡

 

የፈረንጆቹ የገና በዓል የተለያዩ ስጦታዎች የሚሰጡበት በመሆኑ ይህንን እድል በመጠቀም ምርቶች እንዲተዋወቁ አውደ ርዕዩ መሰናዳቱን የሳራ ኔክስት ፋሽን ዲዛይን መስራች ሳራ መሀመድ ተናግረዋል፡፡ 

ree

በአውደ ርዕዩ በተለያዩ ምርቶች ንግድ ላይ የተሰማሩ ሴቶች እንደሚሳተፉ እና ልምድ የሚለዋወጡበትም እንደሚሆን ይጠበቃል ብለዋል፡፡

 

ይህንንም በመጠቀም ምርቶቻቸውን የሚያስተዋውቁ አምራቾች በገበያ ላይ ያላቸውን ተወዳዳሪነት ለመጨመርና የተሻለ የገበያ እድል እንዲፈጠርላቸውም ያግዛል ተብሏል፡፡

 

የኤልቬዜት ኢንተርናሽናል ኤቨንት ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ሩት ኃይሉ በበኩላቸው  የተዘጋጀው አውደ ርዕይ ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ መሆኑንና በዓይነቱ ለየት ባለ መልኩ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ላይ በማተኮር የተለያዩ ዝግጅቶች የተሰናዱበት ነው ብለዋል፡፡

 

ዲፕሎማቶች የተለያዩ ኤምባሲ ተወካዮች የንግድ ተቋማት መሪዎች እና በተለያየ ሙያ ላይ ያሉ እንግዶች ይገኛሉ ተብሎም ይጠበቃል ብለዋል፡፡

 

በሦስቱ ተቋማት የተሰናዳው የዲፕሎማቲክ አውደ ርዕይ ከመጪው ህዳር 19-21 2018  ዓ.ም በዲሊኦፖል ሆቴል የሚካሄድ ሲሆን ኢትዮጵያን የሚያስተዋውቁ የተለያዩ ምርቶች የሚቀርቡበት እንደሆነም ሰምተናል፡፡

 

ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….

 

ምህረት ስዩም

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇

 

 

Recent Posts

See All
በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡

ታህሳስ 6 2018 በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ የአካባቢው ቡሣ ጎኖፋ ወይም የእርዳታ ማስተባበሪያ በበኩሉ ድጋፍ እንዲቀጥል ለሚመለከተው የበላይ አካል ባሳውቅም ድጋፍ ግን ሊቀጥል አልቻለም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page