top of page

ለመጪው ሀገራዊ ምርጫ ለመራጭነት ካርድ የወሰዱ አካል ጉዳተኞች ከእቅዱ 3 በመቶ ብቻ መሆናቸውን የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ተናገረ፡፡

  • 3 hours ago
  • 1 min read

ሚያዝያ 22/2018


ለመጪው ሀገራዊ ምርጫ ለመራጭነት ካርድ የወሰዱ አካል ጉዳተኞች ከእቅዱ 3 በመቶ ብቻ መሆናቸውን የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ተናገረ፡፡

አካል ጉዳተኞች አጠቃላይ ከማህበረሰቡ ከ17 በመቶ በላይ መሆናቸው ይነገራል፡፡


ከመካከላቸው 5 ሚሊየኑ የምርጫ ካርድ ይወስዳሉ ተብሎ ቢጠበቅም የወሰዱት ግን 167,000 ብቻ ናቸው ሲል ፌዴሬሽኑ ነግሮናል።



የምርጫ ካርድ የወሰዱ አካል ጉዳተኞች ቁጥር ዝቅተኛ የሆነበት የመረጃ ክፍተት ምክንያት አንዱ እንደሆነም ተነግሯል።


ይህን የነገሩን የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይነህ ጉጆ አብዛኛው አካል ጉዳተኛ የምርጫ ካርድ አለመውሰድ ጋር በተያያዘ ቅሬታችንን ለምርጫ ቦርድ አቅርበናል፤ እንደ ሃሳብ ያቀረብነውም የመራጮች ምዝገባ እንዲራዘም የሚል ነበር ነገር ግን በምርጫ ቦርድ በኩል ተቀባይነት አላገኘንም ብለዋል።


በሌላ በኩል ለተመራጭነት የቀረቡ እጩ አካል ጉዳተኞች ቁጥር ደግሞ ከባለፈው የምርጫ ዘመን አንፃር ከፍተኛ እንደሆነም ሰምተናል።


በ7ኛው ሃገራዊ ምርጫ ከ250 በላይ አካል ጉዳተኞች ለመመረጥ እንደተመዘገቡ የፌዴሬሽኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይነህ ነግረውናል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..



ፍቅሩ አምባቸው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Recent Posts

See All
አቢሲንያ ባንክ ˝እችላለሁ˝ 5ኛ ዙር የ2025 BYD Seagull ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪና የሎተሪ እድለኛን ለመለየት የእጣ ማውጠት ስነ ስርዓት አከናወነ፡፡

ሚያዝያ 22/2018 አቢሲንያ ባንክ ˝እችላለሁ˝ 5ኛ ዙር የ2025 BYD Seagull ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪና የሎተሪ እድለኛን ለመለየት የእጣ ማውጠት ስነ ስርዓት አከናወነ፡፡ ዛሬ በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት መድረክ ከ2.3 ሚሊዮን በላይ የኩፖን ቁጥሮችን መሠረት በማድረግ የ2025 BYD Seagull ዘመናዊ የ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page