top of page

ህዳር 30፣ 2015- ቡና ባንክ ጠቅላላ ሀብቴ ወደ 34.1 ቢሊየን ብር አድጓል አለ፡፡

  • sheger1021fm
  • Dec 9, 2022
  • 1 min read

ህዳር 30፣ 2015


ቡና ባንክ ጠቅላላ ሀብቴ ወደ 34.1 ቢሊየን ብር አድጓል አለ፡፡


ባንኩ በዘንድሮ የስራ ዘመን 1.25 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን ተናግሯል፡፡


ቡና ባንክ ተቀማጭ የገንዘብ መጠኑ በ6.7 ቢሊየን አድጎ 27.2 ቢሊየን ብር መድረሱን ሰምተናል፡፡


በበጀት ዓመቱ 7.6 ቢሊየን ብር ብድር ሰጥቻለሁ ብሏል፡፡


ባንኩ በጠቅላላ 25.85 ቢሊየን ብር ብድር መስጠቱን ከሪፖርቱ አንብበናል።


በዘንድሮ አፈፃፀም 149.1 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ሰብስቧል ይህ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር ዝቅተኛ መሆኑን ሰምተናል፡፡


የመክፈያ ጊዜ ያለፈባቸው ብድሮች ከጠቅላላ ብድር ያላቸው ምጣኔ 4.1 ነው።


ይህም ብሔራዊ ባንክ ካስቀመጠው የ5 በመቶ ጣሪያ ያነሰ ሆኖ መመዝገቡን ቡና ባንክ ተናግሯል፡፡


ተህቦ ንጉሴ

ree


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
ህዳር 25 2018 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሁለት ሚኒስትሮችን እና የአንድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሹመትን አፀደቀ።

ሹመታቸው በምክር ቤቱ የፀደቀላቸው የሠላም ሚኒስትሩ አቶ መሃመድ እድሪስ፤ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቢንያም ኤሮ ናቸው። አቶ መሃመድ እድሪስ የሰላም ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተሹመው  ስራ የጀመሩት ኀዳር 18 ቀን

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page