top of page

ህዳር 3፣ 2017 - በካፒታል ገበያ እና ኢንቨስትመንት እድል ዙሪያ የተሻለውን ያመጣል የሚል ሰፊ አለም አቀፍ ጉባኤ አዲስ አበባ ልታስተናግድ ነው

  • sheger1021fm
  • Nov 12, 2024
  • 1 min read

Updated: Nov 14, 2024

የተሳከረውን የሪል ስቴት ገበያ መፍትሄ ያቀርባል የተባለው በኦዲተሮችና በሂሳብ ባለሙያዎች ሀሳብ ያዋጣል የተባለ እንዲሁም በአጠቃላይ በካፒታል ገበያ እና ኢንቨስትመንት እድል ዙሪያ የተሻለውን ያመጣል የሚል ሰፊ አለም አቀፍ ጉባኤ አዲስ አበባ ልታስተናግድ ነው፡፡


ይህ አለም አቀፍ ጉባኤ ከሀገር ውስጥ የብሔራዊ ባንክን፣ የገንዘብ ሚኒስቴርን እንዲሁም ከውጪ የአለም ባንክን የአፍሪካ ልማት ባንክና ዩኤንዲፒ(UNDP)ን እንደሚያሳትፍ ከአዘጋጆቹ ሰምተናል፡፡


በዚህ ጉባኤ የካፒታል ገበያው ቁጥጥር እንዲበረታ ዘላቂ የፋይናንስ ስርአት እንዲኖር ይመከርበታል ተብሏል።


አለም አቀፍ ልምድና ተሞክሮው ምንድነው? ፊንቴክና የቴክኖሎጂ ፈጠራ ከገበያው ጋር እንዴት ይጣጣማል በሚለው ጉዳይ ሀሳብ ይዋጣበታል ተብሏል።


ይህ አለም አቀፍ ጉባኤ ለሶስት ቀን እንደሚቆይ ከአዘጋጆቹ ሰምተናል።


በኢትዮዽያ ካፒታል ገበያ ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት አቶ ዮሐንስ አረጋ፤ ከዚህ ጉባኤ የሚነሱት ሀሳቦችና ልምዶች ለገበያው ጥንካሬና ቁጥጥር የሚያዋጣው እንዳለ ለሸገር 102.1 ራዲዮ ነግረዋል።


ተህቦ ንጉሴ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page