top of page

ህዳር 28፣ 2015የእስራኤሉ የፍትህ ሚኒስትር ጌዲዮን ሳር ለሊኩድ የፖለቲካ ማህበር መሪው ለቤኒያሚን ኔታንያሁ የመንግስት ማዋቀሪያ ተጨማሪ ጊዜ ሊፈቀድላቸ

ህዳር 28፣ 2015


የእስራኤሉ የፍትህ ሚኒስትር ጌዲዮን ሳር ለሊኩድ የፖለቲካ ማህበር መሪው ለቤኒያሚን ኔታንያሁ የመንግስት ማዋቀሪያ ተጨማሪ ጊዜ ሊፈቀድላቸው አይገባም አሉ፡፡


የፍትህ ሚኒስትሩ ጥያቄውን ለአገሪቱ ፕሬዝዳንት ይሳቅ ሄርሶግ እንዳቀረቡ ሚድል ኢስት ሞኒተር ፅፏል፡፡


ኔታንያሁ ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡


አዲስ መንግስት እንዲመሰርቱም እስከ መጪው እሁድ ጊዜ ተሰጥቷቸዋል፡፡


ቤኒያሚን ኔታንያሁ እስካሁን አዲሱን መንግስት የመመስረት ጥረታቸው ዳር አልደረሰላቸውም፡፡


ከተሳካላቸው የኔታንያሁ አዲሱ መንግስት እጅግ ቀኝ ዘመም ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡


የፍትህ ሚኒስትሩም ለኔታንያሁ ተጨማሪ ጊዜ እንዳይፈቀድላቸው የጠየቁት በዚሁ ምክንያት ነው ተብሏል፡፡


የኔነህ ከበደ



ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz


bottom of page