top of page

ህዳር 28፣ 2015የእስራኤሉ የፍትህ ሚኒስትር ጌዲዮን ሳር ለሊኩድ የፖለቲካ ማህበር መሪው ለቤኒያሚን ኔታንያሁ የመንግስት ማዋቀሪያ ተጨማሪ ጊዜ ሊፈቀድላቸ

  • Dec 7, 2022
  • 1 min read

ህዳር 28፣ 2015


የእስራኤሉ የፍትህ ሚኒስትር ጌዲዮን ሳር ለሊኩድ የፖለቲካ ማህበር መሪው ለቤኒያሚን ኔታንያሁ የመንግስት ማዋቀሪያ ተጨማሪ ጊዜ ሊፈቀድላቸው አይገባም አሉ፡፡


የፍትህ ሚኒስትሩ ጥያቄውን ለአገሪቱ ፕሬዝዳንት ይሳቅ ሄርሶግ እንዳቀረቡ ሚድል ኢስት ሞኒተር ፅፏል፡፡


ኔታንያሁ ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡


አዲስ መንግስት እንዲመሰርቱም እስከ መጪው እሁድ ጊዜ ተሰጥቷቸዋል፡፡


ቤኒያሚን ኔታንያሁ እስካሁን አዲሱን መንግስት የመመስረት ጥረታቸው ዳር አልደረሰላቸውም፡፡


ከተሳካላቸው የኔታንያሁ አዲሱ መንግስት እጅግ ቀኝ ዘመም ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡


የፍትህ ሚኒስትሩም ለኔታንያሁ ተጨማሪ ጊዜ እንዳይፈቀድላቸው የጠየቁት በዚሁ ምክንያት ነው ተብሏል፡፡


የኔነህ ከበደ



ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz


Recent Posts

See All
የሐምሌ 23 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ግብፅ በግብፅ የሜዴትራኒያን የባህር ዳርቻ የነበረ የአሜሪካ የጋዝ ማጠራቀሚያ መርከብ በድሮን ተመታ ተባለ፡፡ ሁለት የደህንነት ምንጮች መርከቡ በድሮን እንደተመታ አረጋግጠውልኛል ሲል ሬውተርስ ፅፏል፡፡ መርከቡ በድሮን እንደተመታ በእሳት መያያዙ ታውቋል፡፡ ቃጠሎው ወደ ሌላ መርከብም ተጋብቶ ነበር ተብሏል፡፡ ኋላ ግን

 
 
 
የሐምሌ 22 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#አሜሪካ አሜሪካ እና ሳውዲ አረቢያ ኢራቅ ውስጥ በአፍቃሪ ኢራን ታጣቂዎች ይዞታ ላይ ድብደባ ፈፀሙ፡፡ ሰሞኑን ሳውዲ አረቢያ በኢራቅ የሚገኙ አፍቃሪ ኢራን ታጣቂዎች በድሮን ጥቃት አድርሰውብኛል ስትል እንደነበር አልጀዚራ አስታውሷል፡፡ ሳውዲ ጥቃቱን ከማውገዝ በተጨማሪ መበቀሌ አይቀርም በሚል ዝታ ነበር፡፡ በኢራቆቹ አ

 
 
 
የሐምሌ 21 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ጃፓን የጃፓን ደቡባዊ ምዕራብ ክፍል በርዕደ መሬት ተመታ፡፡ ርዕደ መሬቱ የደረሰው ኩማማቶ የተባለው የአገሪቱ ክፍል እንደሆነ ኒኪ እስያ ፅፏል፡፡ የመሬት ነውጡ የተቀሰቀሰው ከምድር በ10 ኪሎ ሜትር ጥልቀት መሆኑ ታውቋል፡፡ ነውጡ በርዕደ መሬት መለኪያ /ሬክተር ስኬል/ 7 ነጥብ 1 ሆኖ መመዝገቡ ታውቋል፡፡ ቀደም ሲ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page