top of page

ህዳር 18፣2017 - የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጠራው ይፋዊ የኦዲት ሪፖርት ውይይት ላይ የመገኘት ግዴታ ቢኖርባቸውም ሳይገኙ ቀሩ

  • sheger1021fm
  • Nov 27, 2024
  • 1 min read

የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በጠራው ይፋዊ የኦዲት ሪፖርት ውይይት ላይ የመገኘት ግዴታ ቢኖርባቸውም ሳይገኙ ቀሩ፡፡


#የኢሚግሬሽንና_ዜግነት_አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት በውይይቱ ላይ አለመገኘታቸው ቋሚ ኮሚቴውን አስቆጥቷል፡፡


የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ቋሚ ኮሚቴው የ2015 እና 2016 በጀት ዓመት የፓስፖርት አገልግሎት አሰጣጥና ውጤታማነትን በተመለከተ የክዋኔ የኦዲት ሪፖርት እና የ2015 በጀት ዓመት የሒሳብ ኦዲት ሪፖርት ላይ ለመወያየት በጠራው ስብሰባ ላይ የመገኘት ግዴታ ቢኖርባቸውም ሳይገኙ ቀርተዋል፡፡

ree

የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ ‘’ምክር ቤቱ ተመርምረው የቀረቡለትን የዋና #ኦዲት_ሪፖርት በይፋ ውይይት በሚያደርግበት ወቅት የመስሪያ ቤቱ የበላይ ሀላፊ የመኖር ግዴታ አለበት’’ ብለዋል፡፡


‘’የመጣችሁትን የስራ ሀላፊዎች ሀላፊነታችሁን አክብራቹሀል’’ ያሉት ሰብሳቢዋ ‘’ነገር ግን የመስሪያ ቤቱ ዋና ሀላፊ በኦዲት ሪፖርት ምርመራ ላይ የመገኘት ግዴታ አለባቸው’’ ሲሉም ተናግረዋል፡፡


‘’ዋና ሀላፊዋ ሀገር ውስጥ የሉም’’ ያሉት ሰብሳቢዋ ‘’ነገር ግን #ደብዳቤያችን ከደረሳቸው በኋላ ነው ከሀገር የወጡት ይህ ድርጊትም ተገቢ እንዳልሆነ ማሳወቅ እፈልጋለሁ’’ ብለዋል፡፡


ይህም ድርጊት የሚያሳየው ለመስሪያ ቤቱ የሰጣችሁትን ትኩረት ነው ብለዋል፡፡


‘’ይህን ፈፅሜአለሁ ይህን አልፈፀምኩም ብሎ ፊት ለፊት ማስረዳት ከ1 የስራ ሀላፊ የሚጠበቅ ነው ብለው ከዚህ በኋላ ይህ ድርጊት እንዳይፈፀም እንድታሳውቁልን እፈልጋለሁ’’ ሲሉ አሳስበዋል፡፡


የመስሪያ ቤቱ የስራ ሀላፊዎችም ይህ ድርጊት ከዚህ በኋላ እንደማይደገም ቃል በመግባት ይቅርታም ጠይቀዋል፡፡


ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Recent Posts

See All
ታህሳስ 3/2018 የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሃይል ፍጆታ ካለፈው ሃምሌ ወር ወዲህ እያደገ መጥቷል ተባለ።

ኢትዮጵያ ከተለያዩ ምንጮች ከምታመርተው የኤሌክትሪክ ሃይል 90 በመቶው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል እንደሆነ ተጠቅሷል። በዘንድሮው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አራት ወራት ኢትዮጵያ ከውሃ እና ከነፋስ ከ15,300 ጊጋዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨቷ ተነግሯል። በየወሩ በአማካይ 3,800 ጊጋዋት ሰአት የኤ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page