top of page

ህዳር 10፣2017 - በኢትዮጵያ ለበይነ መረብ ፆታዊ እና ወሲባዊ ጥቃት የሚጋለጡ ህፃናት ቁጥርም እየጨመረ ነው ተብሏል

  • sheger1021fm
  • Nov 19, 2024
  • 1 min read

ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት በሁሉም ረገድ የወላጅ ወይም የአሳዳጊ ክትትል እና ቁጥጥር እንደሚያስፈልጋቸው ይታመናል፡፡


ጥናቶች እንደሚያሳዩት በከተሞች ከ12 እስከ 17 ዓመት እድሜ ያላቸው ህፃናት 40 በመቶው የኢንተርኔት ተጠቃሚ ናቸው፡፡


ከመካከላቸው 13 በመቶዎቹ ደግሞ ያለወላጅ ክትትልና ቁጥጥር #ኢንተርኔት ይጠቀማሉ ተብሏል፡፡


ይህም በአለም አቀፍ ደረጃ እየሰፋ ለመጣው የኢንተርኔትን መሰረት ባደረገ የህፃናት ወሲባዊ ብዝበዛ እንዲያጋልጣቸው ስጋቱ ከፍ ያለ ነው ተብሏል፡፡


በኢትዮጵያ ለበይነ መረብ ፆታዊ እና ወሲባዊ ጥቃት የሚጋለጡ ህፃናት ቁጥርም እየጨመረ ነው ተብሏል፡፡


በተለይ እየተለወጠ ከመጣው የዲጂታል ቴክኖሎጂ ጋር በተያያዘ ኢንተርኔትን በመጠቀም የሚደርስ የህፃናት #ወሲባዊ_ብዝበዛ የኢትዮጵያ ትልቁ ስጋት እየሆነ መጥቷል ተብሏል።


ወንጀሉ በሌሎች ያደጉ ሀገራት ላይ በስፋት እንደሚታይ እና ኢንተርኔትን በመጠቀም በተለያዩ #ማህበራዊ_መገናኛ ዘዴዎች ወሲባዊ ነክ ምስሎችን እንዲሁም ጽሁፎችን ለህፃናቱ በማጋራት እና ስሜታቸውን በማነሳሳት የሚፈፀም መሆኑ ይነገራል።


ኢትዮጵያ ይህን ዘመን አመጣሽ ወንጀል እና የህፃናትን የፍትህ ጉዳዮችን በተመለከተ በተለይ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው የህግ ባለሞያዎች ዳኞችን ጨምሮ መስራት እንደሚገባት ተነግሯል።


በቅርቡ ይኸው ስጋት ሆኗል የተባለውን ኢንተርኔትን በመጠቀም የሚፈጸም የህጻናት ወሲባዊ ብዝበዛ ቀድሞ ከወጣው የኢትዮጵያ የወንጀል ህግ ጋር እንዴት ተጣጥሞ ይሰራበታል?


ባለሙያዎችስ ጉዳዩን የሚያዩት ዳኞች ምን ያህል ግንዛቤ አላቸው የሚለው በባለሞያዎች ጥናት ተደርጎበታል።



ምህረት ስዩም

Recent Posts

See All
ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ 

ታህሳስ 11/2018   ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡   የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት መስሪያ ቤት በጉዳዩ ላይ መልስ ለመስጠት አልፈቀደም።   ከመንግስት የሚቀርበውን ድጋፍ ለተፈናቃዮች የሚያከፋፍለውና ሌሎች ስራዎችን የሚሰራው በመንግስት የተቋቋመ ኮሚ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page