top of page

ህዳር 10፣2017 - ‘’በመርካቶ ግማሹ ግብር እየከፈለ ሌላው የማይከፍልበት አሰራር መኖሩን ተገንዝበናል’’ ከንቲባ አዳነች አቤቤ

  • sheger1021fm
  • Nov 19, 2024
  • 1 min read

‘’በመርካቶ ግማሹ ግብር እየከፈለ ሌላው የማይከፍልበት አሰራር መኖሩን ተገንዝበናል’’ ከንቲባ አዳነች አቤቤ


‘’በመርካቶ ግማሹ ግብር እየከፈለ ሌላው የማይከፍልበት አሰራር መኖሩን ከነጋዴዎች ጋር ባደረግነው ውይይት እና ክትትል ተገንዝበናል’’ ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ፡፡


‘’ #በመርካቶ ህጋዊ ግብይት እንዲደረግና ለእያንዳንዱ ግብይት ነጋዴው #ደረሰኝ እንዲቆርጥ ቁጥጥር እና ክትትል በማድረግ ላይ እንገኛለን’’ ሲሉም ተናግረዋል፡፡


እንደ ሀገር ያለውን የግብይት ስርዓት በጥናት ላይ የተደገፈ ክትትል ሲደረግ እንደነበረ አንስተው፤ በርካታ ህገ ወጥ የሆኑ አሰራሮች እንደተገኙም አስረድተዋል፡፡

‘’ለእያንዳንዱ ግብይት ደረሰኝ እንዲቆርጡ በማድረግ ግብርን በአግባቡ መሰብሰባችንን አጠናክረን እንቀጥላለን’’ ብለዋል፡፡

ree

ከንቲባ አዳነች ከ #ትራንስፖርት ጋር ተያይዞ ለተነሱ ጥያቄችም ምላሽ ሰጥተዋል፡፡


በከተማዋ የታሪፍ ማሻሻያ ከተደረገ በኋላ፤ ከታሪፍ በላይ ባሰከፈሉ 1,066 አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ ተወስዶባቸዋልም ብለዋል፡፡


በተጨማሪም በተሸከርካሪዎች ውስጥ ታሪፍ መጠን ሳይለጥፉ የቀሩ 4,020 ተሸከርካሪዎችም ተቀጥተዋል ተብሏል፡፡


ከንቲባ አዳነች ይህንን የተናገሩት የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት በ4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤው እያደረገ ባለበት መድረክ ነው፡፡


ማንያዘዋል ጌታሁን

Recent Posts

See All
ታህሳስ 3/2018 የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሃይል ፍጆታ ካለፈው ሃምሌ ወር ወዲህ እያደገ መጥቷል ተባለ።

ኢትዮጵያ ከተለያዩ ምንጮች ከምታመርተው የኤሌክትሪክ ሃይል 90 በመቶው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል እንደሆነ ተጠቅሷል። በዘንድሮው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አራት ወራት ኢትዮጵያ ከውሃ እና ከነፋስ ከ15,300 ጊጋዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨቷ ተነግሯል። በየወሩ በአማካይ 3,800 ጊጋዋት ሰአት የኤ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page