top of page

መስከረም 23፣2017 - ለዝቅተኛ ደመወዝ ተከፋይ የመንግስት ሰራተኞች የኑሮ ጫናውን መቋቋም እንዲችሉ የተደረገው የደመወዝ ጭማሪ በካቢኔ ፀደቋል ተባለ

  • sheger1021fm
  • Oct 3, 2024
  • 1 min read

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያን ተከትሎ ለዝቅተኛ ደመወዝ ተከፋይ የመንግስት ሰራተኞች የኑሮ ጫናውን መቋቋም እንዲችሉ የተደረገው የደመወዝ ጭማሪ በካቢኔ ፀደቋል ተባለ፡፡


የደመወዝ ማሻሻያው ከያዝነው መስከረም ወር ጀምሮ ይተገበራልም ተብሏል፡፡


ይህን ያሉት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ ናቸው፡፡


ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ትግበራ አስመልክተው በሰጡት ማብራርያ ነው፡፡


ለደመወዝ ጭማሪው ከ91 አስከ 92 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት የሚጠይቅ ነው ብለዋል የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ፡፡


ይህም በተጨማሪ በጀትነት የሚታወጅ ይሆናል ተብሏል፡፡


የደሞዝ ጭማሪው የፀጥታ አስከባሪ ተቋማት ሰራተኞችን ጨምሮ በአጠቃላይ ለመንግስት ሰራተኛው የኑሮውን ጫናውን ለማቃለል ታስቦ መንግስት የተገበረው ነው ሲሉ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡


የደመወዝ ጭማሪው በቅርቡ በሲቪል ሰረቪስ ኮሚሽን በኩል ይፋ እንደሚደረግ የገንዘብ ሚኒሰቴር አስርድቷል፡፡



ያሬድ እንዳሻው

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page