በኦሮሚያ ክልል የሚከሰቱ የበሽታ ወረርሽኞችን እና አጣዳፊ የምግብ እጥረት ችግሮችን ለመከላከል የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ ሆነ።
- 3 minutes ago
- 1 min read
ሚያዝያ 15/2018
በኦሮሚያ ክልል የሚከሰቱ የበሽታ ወረርሽኞችን እና አጣዳፊ የምግብ እጥረት ችግሮችን ለመከላከል የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ ሆነ።
ይህንን ፕሮጀክት ይፋ ያደረገው ፈያ ኢንተግሬትድ ዴቬሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን ሲሆን ፕሮጀክቱ ለ6 ወር እንደሚቆይ እና 4.5 ሚሊዮን ዶላር እንደተመደበለትም ሰምተናል።

የድርጅቱ መስራች እና ዋና ዳይሬክተር አንበሱ ቶላ (ዶ/ር) እንዳሉት ይህ ባለብዙ ዘርፍ የአስቸኳይ ጊዜ ምላሽ ፕሮጀክት በጤና፣ በሥርዓተ-ምግብ እና በንፁህ መጠጥ ውሃ ዘርፎች ላይ ያተኮረ ነው ሲሉ ነግረውናል።
የ4.5 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የተመደበለት ፕሮጀክቱ ለዚህም በአሜሪካ መንግሥት የሚደገፈው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ ፈንድ (EHF) ድጋፍ አድርጓል።
የፕሮጀክቱ ዋና ግብ በኦሮሚያ ክልል 5 ዞኖች በተመረጡ 7 ወረዳዎች ውስጥ ለሚገኙ 295 ሺህ ገደማ የሚሆኑ ተጋላጭ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ፤ በችግር ምክንያት የሚከሰቱ የህመም እና የሞት መጠኖችን ፈጣን ምላሽ በመስጠት መቀነስ ነው ተብሏል።
ፈያ ኢንተግሬትድ ዴቬሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን ከ24 ዓመታት በላይ የተቸገሩ ሰዎቸን ሲያግዝ የቆየ ሀገር በቀል የልማት ድርጅት ነው።
በዛሬው ዕለት 17ኛ ጠቅላላ ጉባዔውን እያደረገ ይገኛል።
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ……
ማርታ በቀለ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments