top of page

ሐምሌ 4፣ 2016 - የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ

  • sheger1021fm
  • Jul 11, 2024
  • 1 min read

የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ፡፡


ከዛሬ ሐምሌ 3፣ 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ከአውሮፕላን ነዳጅ በስተቀር በቤንዚን፣ በኬሮሲን፣ በነጭ ናፍጣ፣ በቀላል ጥቁር ናፍጣ እና በከባድ ጥቁር ናፍጣ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ተደርጎል።

የአለም ገበያ ላይ እየታየ ያለውን የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ መሠረት በማድረግ መጠነኛ የመሸጫ ዋጋ ማስተካከያ ማድረግ አስፈልጓል ሲል የነግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡


በዚህም መሰረት:-


ቤንዚን ከነበረበት  78.67 ብር በሊትር  ወደ ብር 82.60 በሊትር ክፍ ብሏል፡፡


ነጭ ናፍጣ ከነበረበት 79.75 ብር በሊትር  83.74 ብር በሊትር ሆኗል፡፡

ኬሮሲን ….  83.74ብር በሊትር


የአውሮፕላን ነዳጅ …  70.83 ብር በሊትር


ቀላል ጥቁር ናፍጣ……  65.48 ብር በሊትር


ከባድ ጥቁር ናፍጣ……… 64.22 ብር በሊትር ሆኗል።


ንጋቱ ሙሉ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page