top of page

ጳጉሜ 1፣2015 - ለመንግስት የሚቀርበው የወርቅ ምርት ከዓመታት በፊት ከነበረው በ92 በመቶ ቀንሷል ተባለ


በሰላም እጦትና በተለያየ ችግር ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ለመንግስት የሚቀርበው የወርቅ ምርት ከዓመታት በፊት ከነበረው በ92 በመቶ ቀንሷል ተባለ፡፡


በዚህም ከ2002 እስከ 2004 ባሉት ዓመታት ወደ 800 ከሎ ግራም የሚደርስ ወርቅ ከአካባቢዎቹ ወደ ብሔራዊ ባንክ ይላክ የነበረ ሲሆን ዘንድሮ የተላከው የወርቅ መጠን ግን ከ67 ኪሎ ግራም ያልበለጠ እንደሆነ ከክልሉ ሰምተናል፡፡


በአካባቢው ወርቅ የኮንትሮባንድ ንግድ ሲሳይ መሆኑም እየተነገረ ነው፡፡


ማንያዘዋል ጌታሁን ያሰናዳውን በእጹብድንቅ እስጢፋኖስ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

bottom of page