top of page

ጥቅምት 7 2018 - በዘንድሮው የትምህርት ዘመን ሰባት ዩኒቨርሲቲዎች በሬሚዲያል መርሀ-ግብር ተማሪዎች እንደማይቀበሉ ተነገረ

  • sheger1021fm
  • Oct 17
  • 1 min read

በዘንድሮው የትምህርት ዘመን ሰባት ዩኒቨርሲቲዎች በሬሚዲያል መርሀ-ግብር ተማሪዎች እንደማይቀበሉ ተነገረ፡፡


ይህንን ያለው ትምህርት ሚኒስቴር ነው፡፡


ሚኒስቴሩ በ2017 ዓ.ም የ12 ክፍል ፈተና ተፈትነው በሬሚዲያል መርሀ-ግብር የማለፊያ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምርጫቸውን የሚያስተካክሉበት ቀንን ይፋ አድርጓል፡፡

ree

በእዚህ መሰረት ተማሪዎች የተቋም ምርጫቸውን እስከ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ( https://student.ethernet.edu.et/ ) በመግባት ማስተካከል እንደሚችሉ ተናግሯል፡፡


የተቋም ምርጫ የሚደረገውም በየትምህርት ቤቶች በተወከሉ መምህራን በኩልም ነውም ብሏል፡፡


በሀገሪቱ ከሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥም ሰባቱ በሬሚዲያል መርሀ-ግብር ተማሪዎች እንደማይቀበሉም ተነግሯል፡፡


ተማሪዎች አይቀበሉም የተባሉት፤ ሀዋሳ የኒቨርሲቲ፣ ጅማ የኒቨርሲቲ፣ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እና አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ናቸው ብሏል ትምህርት ሚኒስቴር በማህበራዊ የትስስር ገፁ ባጋራው መረጃ።


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page