top of page

የኢትዮጵያ ባንኮች አቅም እንዲኖራቸው እና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ይዋሃዱ ዘንድ ተመክረዋል።

  • 2 days ago
  • 1 min read

መጋቢት 9/2018


የኢትዮጵያ ባንኮች አቅም እንዲኖራቸው እና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ይዋሃዱ ዘንድ ተመክረዋል።


ግን ባንኮች እንዴት በመርጅ ኤንድ አክዩዜሽን ይዋሀዱ የሚለውን መስመር ለማሳየት ብሔራዊ ባንክ መንገድ መለየቱ ተሰምቷል።


አንዱ ባንክ እንዴት ሌላኛውን ይግዛው? የሚል የህግ ማዕቀፍ እየተዘጋጀ እንደሆነ የብሔራዊ ባንክ ተናግሯል።


ይህም የሐገር ቤት ንግድ ባንኮች አቅም እንዲኖራቸው እና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ፤ አንዱ ባንክ እንዴት ሌላኛውን መግዛት እንደሚችል የሚያግዝ የህግ ማዕቀፍ ነው።

በዚህ ጉዳይ የጠይቅናቸው የብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ይህ እየተዘጋጀ ያለው መንገድ ባንኮች እንዲዋሀዱ ይረዳቸዋል ብለዋል።


በተያያዘ ወሬ ፤ በኢትዮጵያ የውጭ ባንኮች በተለያየ አማራጭ ገብተው እንዲሰሩ ከተፈቀደ በኋላ አንዳንድ የውጭ ባንኮች የሀገር ውስጥ የንግድ ባንኮችን ሼር ገዝተው ወደ ስራ ለመግባት ከባንኮች ጋር እየተነጋገሩ መሆኑም ተሰምቷል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..


ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page