top of page

ጥር 27፣2017 - ህጋዊ አይደለም በሚል በፍርድ ቤት የተሻረውና የቤትና ቦታ ግብር በጊዜ ክፍሉ ሲል የገቢዎች ቢሮ አሳሰበ፡፡

  • sheger1021fm
  • Feb 4
  • 1 min read

ህጋዊ አይደለም በሚል በፍርድ ቤት የተሻረውና በተለምዶ የጣራና ግድግዳ እየተባለ የሚጠራውን የቤትና ቦታ ግብር ያለቅጣትና ወለድ በጊዜ ክፍሉ ሲል አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አሳሰበ፡፡


በአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ ሚያዚያ 3 ቀን 2015 በጻፈው ድብደቤ #የጣራና_ግድግዳ እየተባለ የሚጠራውን የቤትና ቦታ ግብር ሁሉም ክፍለ ከተሞች እንዲሰበስቡ ትዕዛዝ ማስተላለፉ ይታወሳል፡፡


እናት ፓርቲ ይህንን የፋይናንስ ቢሮን ውሳኔ ሕግን ያልተከተለ፣ የከተማ አስተዳደሩም ባልተሰጠው ስልጣን ነው ስራ ላይ ያዋለው በሚል ውሳኔው እንዲሻር በፍርድ ክርክር ሲያደርግ ቆይቷል፡፡


ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል ከፍተኛ #ፍርድ_ቤት ልደታ ምድብ የፌዴራል አስተዳደር ሥነ ሥረዓት ፍትሐብሔር ችሎት የከተማ አስተዳደሩ ያወጣው የጣሪያ እና ግድግዳ ግብር መመሪያን ባልተሰጠ ስልጣን የወጣ ነው፣ ህጋዊም አይደልም በሚል መመሪያውን እንደሻረው ፓርቲው በትናንትናው እለት በሰጠው መግለጫ ተናግሯል፡፡


ምንም እንኳ ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ቢሽረውም በአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የጣራና ግድግዳ እየተባለ የሚጠራ የቤትና ቦታ ግብር የሚከፍሉ ግብር ከፋዮች ግብሩ ያለቅጣትና ወለድ የሚከፈልበት ጊዜ እየተጠናቀቀ መሆኑን ተገንዝባችሁ ከወዲሁ ግብራችሁን ክፈሉ ሲል ጠይቋል፡፡

ree

በአዲስ አበባ ከተማ 429,829 ግብር ከፋዮች የቤትና ቦታ ግብር ክፍያ እንዲፈፅሙ ይጠበቃል ሲል ቢሮው አስረድቷል፡፡


ይሁንና እስካሁን የከፈሉት ከሚጠበቁት ግማሽ ያህሉ ወይም 228,222 #ግብር ከፋዮች ናቸው ተብሏል፡፡


የቤትና ቦታ ግብራቸውን ከከፈሉ ግብር ከፋዮችም 2.24 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡን ተናግሯል፡፡


ንጋቱ ሙሉ

Recent Posts

See All
ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ 

ታህሳስ 11/2018   ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡   የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት መስሪያ ቤት በጉዳዩ ላይ መልስ ለመስጠት አልፈቀደም።   ከመንግስት የሚቀርበውን ድጋፍ ለተፈናቃዮች የሚያከፋፍለውና ሌሎች ስራዎችን የሚሰራው በመንግስት የተቋቋመ ኮሚ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page