top of page

ግንቦት 26 2017 - ከስርዓተ ምግብ ጋር ተያይዘው የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ውጤታማነታቸው እንዲታይ ቀጥታ ማህበረሰብ ላይ ወርደው መስራት አለባቸው ተባለ

  • sheger1021fm
  • Jun 3
  • 2 min read

ከስርዓተ ምግብ ጋር ተያይዘው በኢትዮጵያ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ዘላቂ እንዲሆኑና ውጤታማነታቸው እንዲታይ ከጥናትና የወረቀት ስራዎች ይልቅ ቀጥታ ማህበረሰብ ላይ ወርደው መስራት አለባቸው ተባለ፡፡


ምንም እንኳን በተለያየ ጊዜ ከአመጋገብ ሥርዓት ጋር በተገናኘ በርካታ ፕሮጀክቶች ቢቀረጹም የታለመላቸውን ሳያሳኩ የሚቋረጡ አሉ ተብሏል፡፡


ለዚህም ስራዎቹ ቀጥታ ማህበረሰብን የሚያካተቱ ሆነው መተግበር ውጤታማ እንዲሆኑ ያደርጋል ሲሉ የነገሩን በኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ላይ የሚሠራው ዘ ሀንገር ፕሮጀክት የኢትዮጵያ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ተሾመ ሽብሩ ናቸው፡፡


አብዛኛዎቹ ኒውትሪሽን ላይ የሚቀረጹ ፕሮጀክቶች ዘላቂነት የሚያጡት ህብረተሰቡ በሚገባ ባለቤት ወይም መሪ ሆኖ ስለማይከናወኑ ነው፤ በአብዛኛው ፕሮጀክቶች የሚወድቁት ህብረተሰቡ በሚገባ ግንዛቤ ፈጥሮ ከዛ በኋላ እኛ ባለሙያ ነን ብለን እዛ የምንሄደው ሳንሆን ራሱ መናገር ሲጀምር ነው ብለዋል፡፡


ቀጥታ ማህበረሰብን በጉዳዩ ላይ በማሳተፍ የሚሰሩ ስራዎች ውጤት ይኖራቸዋል የሚሉት አቶ ተሾመ በተለይ ምግብ አምራች በሆኑ አርሶ አደሮች ላይ ቀጥታ መስራት የተሰባጠረ የምግብ ምርት እንዲኖር በማድረግ ሌሎችንም የሚጠቀም ማድረግ ቢቻልም በኢትዮጵያ ያለው እውነታ ግን በተቃራኒ ነው ይላሉ፡፡

ree

የግብርና የአመራረት ሥርዓታችን ስፔሻላይዝ እያረግን ገበያ ተኮር እየሆነ መምጣቱ አንድ ዓይነት ምርቶች ብቻ መወሰኑ የተለያየ የምርት አለመኖሩ አማራጭ እና የተለያየ የምግብ ስብጥር እንዳይኖር የሚያደርግ ነው ሲሉ አቶ ተሾመ ተናግረዋል፡፡


የሥርዓተ ምግብ ጉዳይ ከጤና በተጨማሪ በትውልድ ላይ የሚሰራበት ቢሆንም የሚያደርሰው ጉዳትም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያርፍ ነው ለዚህም በግል ድርጅቶችም ይሁን በመንግስት የሚቀረፁ የዘርፉ ፖሊሲዎች ከሐሳብ ባለፈ በተግባር የሚታዩ መሆን አለባቸው ሲሉ አቶ ተሾመ ነግረውናል፡፡


በኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ላይ በመንግስት እንዲሁም የለጋሾች ድርጅቶችን ጨምሮ የሚሰሩ በርካታ ፕሮጀክቶች ቢኖሩም በተመጣጠነ ምግብ እጥረት ምክንያት የሚከሰት መቀንጨር ግን ከነበረበት 37 በመቶ ጨምሮ በቅርብ በወጣ ሪፖርት ወደ 39 በመቶ ማሻቀቡ ተነግሯል፡፡


ለዚህም የምግብ ዋጋ መናር፣ ጦርነትና ድርቅ ምክንያት መሆናቸው ተጠቅሷል፤ ለመፍትሄውም ከወቅታዊ ሁኔታዎች ጋር ተጣጥሞ የሚሄድና ውጤታማነቱ የተመዘነ ቀጥታ በማህበረሰብ ላይ የሚተገበር የስርዓተ ምግብ ፖሊሲ እንደሚያስፈልግ ተመክሯል፡፡


ምህረት ስዩም


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page