top of page

ግንቦት 26 2017 - በቡና ላኪነት ለመሰማራት 15 ሚሊዮን ብር ካፒታል ማስያዝ ሊጠይቅ ነው

  • sheger1021fm
  • 2 days ago
  • 1 min read

ከዚህ ቀደም የቡና ላኪነትን የብቃት ማረጋገጫ ለማግኘት ይጠየቅ የነረበው የ1.5 ሚሊዮን ብር በ10 እጥፍ እንዲያድግ የተደረገው ዘርፉ በእውቀትና የተሻለ አቅም ባላቸው ሰዎች እንዲያዝ በማስፈለጉ ነው ተብሏል፡፡


ከዚህ ቀደም በቡና ላኪነት የብቃት ማረጋገጫ ለማግኘት ይጠየቅ የነበረው ካፒታል 1.5 ሚሊየን ብር ነበር፤ ይህ ገንዘብ አሁን በአስር እጥፍ እንዲያግ በኢትዮጵያ ቡና ሻይ ባለስልጣን ማሻሻያ መቅረቡ ተሰምቷል።


የሚጠየቀው ካፒታል አነስተኛ ሆኖ በመቆየቱ አትራፊ ነው በሚል ብቻ ብዙዎች የሚገቡበት ዘርፍ ሆኖ ቆይቷል የሚሉት የኢትዮጵያ ቡና ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ግዛት ወርቁ ናቸው።


ይሄ ደግሞ እዚሁ ሀገር ቤት በአቅራቢ እና ላኪዎች እንዲሁም ላኪዎች እና የውጭ ገዥዎች መካከል ችግሮች እንዲፈጠሩ ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል።


#የቡና_ንግድ ሰዎች የተወሰነ ገንዘብ በአንድ አጋጣሚ ስላገኙ ብቻ የሚገቡበት ሊሆን አይገባም የሚሉት ስራ አስኪያጁ፤ ስለ ዋጋው፣ ጥራቱ እና የአዘገጃጀት ሂደቱ ማወቅ ወሳኝ እንደሆነ ያክላሉ።


የነጻ ገበያ መርህ ሁሉም ሰው በእኩልነት ይወዳደር፤ ገበያው በራሱ አላፊውን እና ከወዳቂው ይለያል የሚል እንደሆነ ያስታወሱት አቶ ግዛት ይሄ ግን በቡና ንግድ ላይ ብዙም እየሰራ አይደለም ብለውናል።


የቡና ላኪነት የብቃት ማረጋገጫ ለማግኘት የሚጠየቅ ማህበር ወይም ግለሰብ ከካፒታሉ በተጨማሪ የአንድ ዓመት የፋይናንስ እንቅስቃሴውን የሚያሳይ በባንክ የተረጋገጠ ሰነድ ማቅረብ እንደሚጠበቅበት ተጠቅሷል።


የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት የወሰደ ቡና ላኪ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ወደ ስራ መግባት እንዳለበትም በመመሪያው ሰፍሯል።


ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ወደ ስራ መግባት ካልቻለ ደግሞ ይህንኑ በማስረጃ አስደግፎ ለቡናና ሻይ ባለስልጣን ማቅረብ ይኖርበታል ተብሏል።


ማሻሻያው የሚመለከታቸው ከመከሩበት በኋላ ስራ ላይ እንደሚውል የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ተናግሯል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….



ንጋቱ ረጋሳ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





コメント


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page