top of page

ግንቦት 26፣2016 - የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እስረኞችን በሃገራዊ ምክክሩ ለማሳተፍ እየሰራሁ ነው አለ

  • Jun 3, 2024
  • 1 min read

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በህግ ጥላ ስር የሚገኙ እስረኞችን በሃገራዊ ምክክሩ ለማሳተፍ እየሰራሁ ነው አለ፡፡


በምክክሩ ሂደት አጀንዳዎችን በማሰባሰብ ላይ የሚገኘው ኮሚሽኑ በተቻለ መጠን ሁሉም ይሳተፋል፤ አንድም የሚቀር የማህበረሰቡ ክፍል የለም ብሏል፡፡


ሁሉም ተሳታፊ፤ ለምክክሩ ይበጃል ሊመከርበትም ይገባል የሚለውን አጀንዳ እያቀረበም ይገኛል፡፡


በተለያዩ ምክንቶች ተጠርጥረው የታሰሩ፤ በተለይም በፖለቲካ እንቅስቃሴቸው ምክንያት የታሰሩ ፖለቲከኞች በአካል ወደ ምክክሩ መጥተው መሳተፍ ስለማይችሉ፤ በምክክሩ እንዴት ይሳተፉ የሚለውን እየተነጋገርበር ነው ያሉን የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ብሌን ገብረ መድህን ናቸው፡፡


በተጨማሪም ኮሚሽነሯ በፖለቲካ ምክንያት የታሰሩ ነገር ግን በአጀንዳነት ይያዝልን የሚሉት ሃሳብ ያላቸው እስረኞች አጀንዳቸውን ከእስር ቤት ሆነው እንዲልኩ ለምን አልተደረገም በሚል ጥያቄ የቀረበላቸው ሲሆን፣ እስረኞቹ በምን መንገድ ይሳተፉ የሚለው ገና አልተወሰነም እየተመከረበት ነው፤ ነገር ግን ሃሳቦቻቸው በፓርቲዎቻቸው በኩል ይካተታሉ ብለዋል፡፡


የኢትዮጵያ ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን ካሳለፍነው ግንቦት 21 ቀን 2016ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታ 7 ቀናት በአዲስ አበባ ሲያካሂድ የቆየው አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት በነገው እለት ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡


ምንታምር ፀጋው



Recent Posts

See All
በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ሊከሰት የሚችለው ኤልኒኖ በግብርና እንዲሁም አምራች እና የአገልግሎት ዘርፎች ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል ተባለ።

ነሐሴ 7 2018 በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ሊከሰት የሚችለው ኤልኒኖ በግብርና እንዲሁም አምራች እና የአገልግሎት ዘርፎች ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል ተባለ። ከአስር ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የታየው የኤልኒኖ ተፅዕኖ የእህል ምርት ውጤትን ከ15 እስከ 20 በመቶ እንዲቀንስ አድርጎ እንደነበር አንድ የዘርፉ ተመራማሪ ነ

 
 
 
የኤሌክትሪክ ታሪፍ በየጊዜው ሲጨምር ይታያል፡፡

ነሐሴ 7 2018 የኤሌክትሪክ ታሪፍ በየጊዜው ሲጨምር ይታያል፡፡ በዚህም ደንበኞች ቅሬታ ያቀርባሉ ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በበኩሉ አዲስ የታሪፍ ጭማሪ አለማድረጉን፤ የአሁኑ የዋጋ ለውጥ ከ2017 ጀምሮ በ16 ዙር ለማስፈጸም የታቀደው አሰራር አካል ነው ብሏል፡፡ እንደውም ከሁለት አመት በፊት ተግባራዊ ያ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page