top of page

ግንቦት 22 2017 - የኤሌትሪክ ተሽከርካሪዎች አምራች እና አከፋፋይ ዶዳይ ማኑፋክቸሪንግ ከአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ጋር አብሬ መስራት ጀመርኩ አለ።

  • sheger1021fm
  • May 30
  • 1 min read

የኤሌትሪክ ተሽከርካሪዎች አምራች እና አከፋፋይ ዶዳይ ማኑፋክቸሪንግ ከአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ጋር አብሬ መስራት ጀመርኩ አለ።


ዶዳይ የሐገሪቱን የኤሌትሪክ ትራንስፖርት አጀንዳ ለመደገፍ ባለኝ ቁርጠኝነት 40 የኤሌክትሪክ ሞተሮች ለአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ሰጥቻለሁ ብሏል።


የተበረከቱት ኤሌክትሪክ -ሞተር ሳይክሎች ከዶዳይ ዘመናዊ የባትሪ መለዋወጫ አውታር ጋር ሙሉ ለሙሉ የተገናኙ ሲሆኑ ከዶዳይ ስማርት ኔትወርክ ጋር የተገናኙ በመሆናቸው፤ አሸክርካሪዎች በስልካቸው ክፍያ እንዲከፍሉ እና ሃይል ያለቀበትን ባትሪያቸውን በ5 ደቂቃ ወዲያውኑ ሙሉ በሙሉ ቻርጅ ባረገ ባትሪ እንዲቀበሉ ያስችላቸዋል ተብሏል ።

ree

ኩባንያው ከአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ጋር ያደረገው ስትራቴጂካዊ ትስስር የከተማ ትራንስፖርትን ለማሳደግ፣ የኤሌትሪክ ተሽከርካሪ ዘላቂነት ለማስተዋወቅ እና ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች አዲስ የስራ እድሎችን ለመፍጠር ያለመ ነው መሆኑ ተጠቅሷል።


የዶዳይ ማኑፋክቸሪንግ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዩማ ሳሳኪ " ከአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ እና ከወሳኝ የከተማ ተቋማት ጋር በመተባበር ስራ በመጀመራችን ደስታ ይሰማናል" ሲሉ መናገራቸው ተሰምቷል ።


የጃፓኑ ዶዳይ ኩባንያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች አምራችና አከፋፋይ ሲሆን አዳዲስ እና ዘላቂ የትራንስፖርት መፍትሄዎችን ለማቅረብ ቁርጠኛ ነኝ ብሏል።


ንጋቱ ሙሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page