ግንቦት 20 2017 -ንጹህ የመጠጥ ውሃ የሚያገኝ ኢትዮጵያዊያን ከ40 በመቶ አይበልጡም፡፡
- sheger1021fm
- 2 days ago
- 1 min read
ንጹህ የመጠጥ ውሃ የሚያገኝ ኢትዮጵያዊያን ከ40 በመቶ አይበልጡም፡፡
በገጠር ደግሞ እስከ 70 በመቶው የንጹህ መጠጥ ውሃ ማግኘት አልቻለም፡፡
እንደ ጎንድር፣ ሻሸመኔ፣ ጌዲዮ እና ሰሜን ወሎን ጨምሮ መሰረታዊ የንጹህ የመጠጥ ውሃ ችግር ያለባቸው የሀገሪቱ ከተሞች እና አካባቢዎች መፍትሄ እንዲሰጣቸው ተጠይቋል፡፡
ታሪካዊ እና ጥንታዊ የሆነችው ጎንደር ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋኗ 21 በመቶ እንደሆነ ተነግሯል፡፡
በኢትዮጵያ ውሃ ዳር የሚኖሩ አካባቢዎች ጭምር ከፍተኛ የመጠጥ ውሃ ችግር እንዳለባቸው የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አባላት ተናግረዋል፡፡
የምክር ቤት አባላቱ ይህን የተናገሩት እና ችግሩ እንዲፈታ የጠየቁት በትናንትናው እለት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከምክር ቤት አባላት ለተነሱለት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በፓርላማ በተሰየመበት ወቅት ነው፡፡
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በበኩሉ የመጠት ውሃ ሽፋንን ላማሳደግ እየሰራ እንዳለ ተናግሮ መስኩ ከፍተኛ ገንዘብ ስለሚጠይቅ ሁሉም ድርሻውን መወጣት አለበት ብለዋል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…….
ያሬድ እንዳሻው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
📌 Linkedin : https://shorturl.at/21bFN
Comments